ርዕሠ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የሸኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል “ቲካሸ ቤንጊ ” እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላለፉ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦች አንዱ የሆነው የሸኮ ብሔር የራሱን የዘመን አቆጣጠር ስልት ጠብቆ ሁነቱን ከሚያከብሩት ብሄረሰቦች ውስጥ አንዱ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል ፡፡ በቤንች ሸኮ ዞን በሸኮ ብሔር ዘንድ የሚከበረው ‹‹ ቲካሽ ቤንጊ›› በአካባቢው የምርት መሰብሰቢያ ወቅት መሰረት በማድረግ፣ የግራዋ ዛፍ ሲያብብ ማር የሚቆረጥበት፣ የተጣላን በማስታረቅ፣ ከተገኘው ምርት በአንድ ላይ ማዕድ…
