ቲኬሻ ቤንጊን ስናከብር አንድነትን፣ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጽናት ለልማት ይበልጥ የምንነሳሳበት ሊሆን ይገባል፦ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የሸኮ ብሔር ዘመን መለወጫ “ቲካሻ ቤንጊ ” በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች ተከብሯል ። በበዓሉ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ቲካሻ ቤንጊ የመተሳሰብና የአንድነት በዓል ነው ሲሉ ተናግረዋል ። የሸኮ ብሔረሰብ በዓሉን ሲያከብር ይበልጥ የወንድማማችነት እና እህትማማችነት እንዲጠናከር የሚያስችል ታሪክና ባህል እንዲጎለብት የሚያስችል ነው ሲሉም ተናግረዋል ። አካባቢው የሰብል ምርት፣የማር ምርት፣የቡና ምርት በስፋት የሚገኝበት በመሆኑ…

Read More

የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የጅማ ከተማን የተደበቀ ውበት ይበልጥ እንዲፈካ አድርጓል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጅማ የነበራቸውን ቆይታ አስመልከተው በሰጡት ማብራሪ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች ሀገር መሆኗን አውስተው÷ ቢሰራባቸው ዓለምን የሚያስደንቁ የተፈጥሮ ጸጋዎች በሁሉም የኢትዮጵያ ጫፍ እንዳሉ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መደመር የሚለው ሃሳብ ሲጀመር ሶስት ዋና ዋና ምሰሶዎች ላይ የቆመ እንደነበር የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ የመጀመሪያው የኢትዮጵያን ተፈጥሮ፣ ጸጋና ሃብት በውል ማወቅ መቻል ነው ብለዋል፡፡ አሁን ላይ የጅማን…

Read More

ከሸኮ ብሔር ቱባ ባህሎችና ታሪካዊ ክዋኔዎች አንዱ የሆነው ፈጣሪ የሚመሰገንበት “ቲካሻ ቤንጊ” የአዲስ ዓመት የምስጋና በዓል እየተከበረ ነዉ።

ቲካሻ ቤንጊ የሸኮ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፣የክልሉ ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታን ጨምሮ የፌዴራል እና የክልል፣የዞን ከፍተኛ አመራሮች ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣ተጋባዥ እንግዶች የሚታደሙበት እንደሆነም ታውቋል። ቲካሻ ቤንጊ የሸኮ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል በኢቢሲ ቀጥታ ስርጭት ከሸኮ የበዓሉ ማክበሪያ ስፍራ የሚተላለፍ…

Read More

በሚዛን አማን ከተማ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ አበረታች መሆኑ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና ትራንስፖርትና የመንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዋ ሳፒን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሚዛን አማንን የኮሪደር ልማት ሥራ ጎብኝተዋል። የክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትራንስፖርትና የመንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዋ ሳፒ እንደገለፁት የኮሊደር ልማት…

Read More

ኢትዮጵያ ከውጪ የምታስገባውን የድንጋይ ከሰል ሙሉ ለሙሉ መተካት የሚያስችሉ ፋብሪካዎች በዚህ ዓመት ወደ ምርት ይገባሉ፦ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኝ

ኢትዮጵያ ከውጪ የምታስገባውን የድንጋይ ከሰል ሙሉ ለሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካት የሚያስችሉ ፋብሪካዎች በተያዘው ዓመት ተጠናቀው ሥራ እንደሚጀምሩ የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኝ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አክሲዮን ማህበር የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀው ስራ አስጀምረዋል፡፡ የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኝ በዚሁ ወቅት…

Read More

የተገለጠ ዓይን ሲኖር የኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ የተቃና ይሆናል:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ዛሬ የጎበኘነው ልማት የሚያሳየው የተገለጠ ዓይን እና የጠራ ሃሳብ ሲኖር በአጠረ ጊዜ ውስጥ ሀገር መቀየር የሚያስችል ዕድል መኖሩን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀው ስራ አስጀምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት፥ እንዲህ ያለው ዕድል ተግቶ የማየት እና የመስራት ልምምድ ሲጨመርበት…

Read More

ቲካሻ ቤንጊ የሸኮ ብሔር የአዲስ ዘመን ብስራት ፣ የምስጋናና ቱባ የአብሮነትና ባህላዊ ክዋኔዎችን የያዘ ነው ፦ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ

2ኛው የሸኮ ብሔር የዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል “ቲካሻ ቤንጊ” የፓናል ውይይት በሸኮ ወረዳ እየተከበረ ነው። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤና የሸኮና አካባቢው ምሁራን የጥናትና ምርምር ማህበር የበላይ ጠባቂ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ የፓናል መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ቲካሻ ቤንጊ የሸኮ ብሔር ለዘመናት ጠብቆ ያቆየው ስለ ዘመን አቆጣጠር ፣ ለታላላቆች ያለውን…

Read More

” በዛሬው እለት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባውን የኢቲ ማዕድን ልማት አ.ማ የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካን መርቀን ስራ አስጀምረናል። ፋብሪካው በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የድንጋይ ከሰል ምርት ከማሻሻል ባሻገር ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል የፈጠረ ነው። “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Read More