በቦንጋ ከተማ የመንገድ ዳር መብራት ሽቦ የሰረቀ ተከሳሽ እና የተሰረቀ ሽቦዎችን ከሌባ የገዛ አንድ ግለሰብ በእስራትና በገንዘብ መቀጣታቸዉን በካፋ ዞን ፍትህ መምሪያ አስታወቀ

ወንጀሉ የተፈጸመው በካፋ ዞን በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ጥር 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከንጋቱ 12:00 ሰዓት በዩንቨርስቲ ቀጠና አበቺ መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን ወንጀሉን የፈፀሙት ታረቀኝ ቆጭቶና ታምራት ወ/ማሪያም መሆናቸዉን የገለፁት በካፋ ዞን ፍትህ መምሪያ የታክስና ኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ዐቃቤ ህግ አንዷአለም አሰፋ ናቸዉ። እንደ ዐቃቤ ህግ አንዷአለም ገለፃ ተከሳሽ ታረቀኝ ቆጭቶ የተባለው በተጠቀሰው ቀን…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የተፋሰስ ልማት ሥራን ጎበኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የተፋሰስ ልማት ሥራን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ፣ የፌደራል እንዲሁም የክልሉ እና የዞኑ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኮሙኒኬሽን ዘዴ ልምድ በማካፈል ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገለጸ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኮሙኒኬሽን ዘዴ በልዩ አተያይ ሐሳቦችን፣ የሥራ ተነሳሽነትን የሚፈጥሩ ልምዶችንና ተግባራትን በማካፈል ላይ ያተኮረ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልሎች የሚገኙ የሥራ ሪፖርቶችን ለሌሎች የተነሣሽነት ምንጭ እንዲሆኑ ሲያጋሩ መቆየታቸውንና ላለፉት ሰባት ዓመታት ለየት ባለ መንገድ ግልጽነትና ተደራሽነትን በማለም የኮሙኒኬሽን ስራው መከናወኑን ጽ/ቤቱ አስታውቋል፡፡ በዚህ ሂደት የክልሎች የሥራ ለውጦች…

Read More

ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግራቸው እየተቀረፈ መሆኑን ነዋሪዎች ተናገሩ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከተመሠረተ ወዲህ ዘመናትን ያስቆጠረ የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግራቸው መቀረፉን የዳውሮ ዞን ዛባ ጋዞ ወረዳ ደቼ ደነባ እና የካፋ ዞን ጠሎ ወረዳ ኦሚያ ቀበሌ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ክልሉ ከተደራጀ ወዲህ በዳዉሮ ዞን ዛባ ጋዞ ወረዳ ደቼ ደነባ ቀበሌ በ12 ሚሊዮን ብር ወጪ 2ሺህ 364 የቀበሌ ነዋሪዎችን እና የእንስሳት ውሃ ማጠጫ ገንዳዎችን ያካተተ…

Read More

የቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ችግር እየገጠማቸው መሆኑን በሸካ ዞን የቴፒ ከተማ ና የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ

የሸካ ዞን ጤና መምሪያ የተገልጋዮች ቅሬታ እውነት መሆኑን አጣርቼ ለእርምት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል። ቅየህብረተሰብ ክፍሎችና ታካሚዎች እንደገለጹት ታክሞ ለመዳን እየመጣን በመፀዳጃ ቤት ጉድለት ላላስፈላጊ በሽታ እየተዳረጉ መሆኑን ገልጸዉ የባለሙያ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር፣የአልጋ ና የመድሀንት እጥረት እንዳለ ገልጸዋል። የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጂ አቶ ተገኝ ገቦ በበኩላቸው ሆስፒታሉ ከ2010 ዓ .ም ወዲህ ከመጀመሪያ ደረጃ ወደ አጠቃላይ ሆስፒታል ማደጉን…

Read More

በየአካባቢው የሚገኙ ሀብቶችን በተገቢው በመጠቀም ምርታማነትን ለማጎልበት በትጋት እየተሰራ እንደሚገኝ

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው አስታወቁ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የተመራው ቡድን በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ ምርት ጉብኝት አካሂዷል። በጉብኝቱ ወቅት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት በክልሉ ምርታማትን ለማጎልበት የሚያስችሉ በርካታ ተፈጥሯዊ ሀብቶች እና አማራጮች አሉ። በተለይም የውሃ ሀብቶችን በተገቢው በመጠቀም እንደ ክልል ከ5 ሺህ…

Read More

ሕብረተሰቡ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎቹን እንዲያቀርብ ጥሪ ቀረበ

ሕብረተሰቡ በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮችና አምራች ዘርፎች ላይ ጥያቄዎቹንና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮችን እንዲያቀርብ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥሪ አቀረበ፡፡ በዚሁ መሠረት ሕብረተሰቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች አማካኝነት ጥያቄዎቹን መላክ እንደሚችል ተገልጿል፡፡ ለሚቀርቡ ጥያቄዎችም የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡበት ጽሕፈት ቤቱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አረጋግጧል፡፡

Read More

የክልሉ ትምህርት ቢሮ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፖርታል በይፋ አስጀመረ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ከኢፌዴሪ ትምህርት ምኒስቴር ጋር በመተባበር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፖርታል በይፋ አስጀመሯል። በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አስተዳደር ታርጫ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተካሄደው ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሃግብር የተገኙ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ባህሩ አለሙ ፕሮጀክቱ የተማሪዎችን የእንግሊዝኛ ክህሎት ከማሻሻልም ባሻገር በውጤት መሻሻል ላይ ያለው…

Read More

መፅሐፍ ቋሚ እውቀትን ለመፍጠርና ከትውልድ ወደትውልድ ለማስተላለፍ አጋዥ መሆኑ ተገለፀ።

የኢትዮጵያ ቤተመጻሕፍት እና ቤተመዛግብት የተለያዩ መጽሐፍት ለምዕራብ ኦሞ ዞን አስረክቧል። በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተመጽሐፍት አገልግሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አባተ ካሳው እንደተናገሩት፤ አገልግሎቱ እውቀትን በማከማቸትና ለሚቀጥለው ትውልድ በማስተላለፍ ለ80 ዓመታት መስራቱን ተናግረዋል። ማንበብ እየፈለጉ መፅሐፍት የማያገኙ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች መኖራቸውን አንስተው፤ አገልግሎቱ በትምህርት፣ በማረሚያ ቤቶችና በህዝብ ቤተመጻሕፍቶች የንባብ ባህልን ለማዳበር እየሰራ ይገኛል ብለዋል። ዛሬ ላይ የተደረገው…

Read More