ቢሮው ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች የሚያደርገውን የስነ ልቦናና የቁሳቁስ ድጋፍ አጠናክሬ እቀጥላለሁ አለ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ በተለያዩ ሁኔታዎች ፆታዊ ጥቃት ሰለባ ለሚሆኑ ሴቶች አገለግሎት የሚውል ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፊ አደረገ። ድጋፉ በክልሉ በሚገኙ በአራቱ ጠቅላላ ሆስፒታሎች የህክምናና የስነ ልቦና እርዳታ ለሚያገኙ ተጠቂ ሴቶች በነፃ የሚደረግ እንደሆነም ተገልጿል። በክልሉ ከሚገኙ ከአራት ጠቅላላ ሆስፒታሎች መካከል አንዱ ለሆነው ለታርጫ ጠቅላላ ሆስፕታል…

Read More

የፍርድ ቤቶች ስራ በዳኝነት አካሉ ብቻ የሚሳካ ባለመሆኑ በየደረጃ የሚገኙ የባለድርሻ አካላት ትብብር፣ ድጋፍና ቅንጅት እንደሚሻ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከስር መዋቅሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በአስር ዓመት መሪ ዕቅድ ክለሳ፣ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል። በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ የዘመናት የህዝብ ቁጭትና…

Read More

የዘንድሮ “ማሽቃሬ ባሮ” በድርርብ ስኬቶች እና ደስታዎች የታጀበ ነው:- አቶ እንዳሻው ከበደ

የ2018 ዓ.ም የካፈቾ ዘመን መለወጫ ማሽቃሮ በዓልን አስመልክቶ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻ ከበደ መግለጫ ሰጥተዋል። በዓሉ ለዓመታት መከበር ካቆመ በኃላ በ1986 ዓ.ም የባህል እና ቋንቋ ስምፖዚዬም መካሄዱን ተከትሎ በ1998 ዓ.ም በድጋሜ መከበር መጀመሩን ያወሱት ዋና አስተዳዳሪው ዘንድሮ በልዩ ድምቀት ድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። በዓሉ ህዝባዊ መሠረት ያለው በመሆኑ ላለፉት 20 ዓመታት ወቅቱ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እያካሄደ ነው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከስር መዋቅሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በአስር ዓመት መሪ ዕቅድ ክለሳ፣ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ ማካሄድ ጀምረዋል። ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት እንደሚደረግ የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል ።…

Read More

የህዳሴውን ግድብ በመጠናቀቁ በክልሉ ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ይካሄዳል:-አቶ የሺዋስ ዓለሙ

የህዳሴውን ግድብ በመጠናቀቁ በክልሉ ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ይካሄዳል:-አቶ የሺዋስ ዓለሙ የዘመናት ህልም፣ የሉዓላዊነት አርማና የ”ይቻላል” መንፈሳችን ማሳያ የሆነው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ህዝቦች በታላቅ ደስታ ላይ ይገኛል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ እንዳስታወቀው፣ ይህን ታሪካዊ ድል በመላው ክልሉ በሚገኙ ከተሞችና ወረዳዎች በደማቅ ህዝባዊ ሰልፎች ለማክበር ዝግጅቱ…

Read More

“ኢትዮጵያውያን ብርቱ ነን”

“ኢትዮጵያውያን ብርቱ ነን” የህዳሴው ግድብ ተገቢውን እውነታ በማስረዳት ለኢትዮጵያ እናቶች ፍትህ እንዲያገኙና ብርሃን እንዲያዩ ማድረግ ችሏል ሲሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገልጸዋል። በዛሬው ዕለት በመስቀል አደባባይ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ሀሳብ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፤ የሁላችንም የአዕምሮ፣ የእውቀት፣ የላብ፣ የደም፣ የጉልበትና ሃብት ውጤት…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን ነገ ይጀምራል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን ነገ ይጀምራል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኙ ሁሉም አካባቢዎች የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ነገ መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ እንደሚጀመር የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ እንደገለጹት፣ የትምህርት ዘመኑን…

Read More

የቦንጋ ከተማ የኮርደር ልማት ሥራ በተሻለ አፈጻጸም እየተከናወነ መኾኑ ተመላከተ።

የቦንጋ ከተማ የኮርደር ልማት ሥራ በተሻለ አፈጻጸም እየተከናወነ መኾኑ ተመላከተ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ የቦንጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ግንባታ ጎብኝተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ከሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመኾን በሁለተኛው ምዕራፍ በቦንጋ ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጉብኝቱም ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በከተማው እየተከናወነ የሚገኘው…

Read More

በሕዳሴ ግድብ የታየው ሕዝባዊ አንድነትና ትብብር በሌሎች ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት

በሕዳሴ ግድብ የታየው ሕዝባዊ አንድነትና ትብብር በሌሎች ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታየው ሕዝባዊ አንድነትና ትብብር በሌሎች ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የመንግሥት አመራሮችና ምሁራን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ መመረቃቸው ይታወቃል። የግድቡን የ14 ዓመት ጉዞ በተለይም የህዝቡን ተሳትፎ…

Read More