ቲካሻ ቤንጊ አሰባሳቢ ፣ አንድነትን ፈጣሪና ባህልና ቋንቋን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ድልድይ መሆኑን የብሔረሰቡ ተወላጆች ተናገሩ።

በዓሉ ሰላምን የማጽናት ፣ ልማትን የማረጋገጥና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን የሚያጠናክር በመሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራው በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አዘጋጅ ኮሚቴው ገልጿል። የሸኮ ብሔር የአዲስ ዘመን ብስራትና የምስጋና በዓል የሆነው ቲካሻ ቤንጊ ለዘመናት ተቋርጦ ከቆየበት ባለፉት 2 አመታት የብሔረሰቡ ተወላጆችና እንግዶች በተገኙበት በሸኮ ከተማ በድምቀት ተከብሯል። የብሔሩ ተወላጆች ከሆኑት ውስጥ አቶ አዲሱ በዲ ፣ ኤፌሶን ሱብሳ ፣…

Read More

የጋንዲዎች ተራራ ላይ ሀይቅ

የጋንዲዎች ተራራ ላይ ሀይቅ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን በአንድራቻ ወረዳ የሚገኝ ሲሆን ከመድናችን አዲስ አበባ 700 ኪ.ሜ ከዞኑ ዋና ከተማ ቴፒ በ35 ኪ.ሜ ላይ ይገኛል፡፡ በክልሉ ሸካ ዞን በአንድራቻ ወረዳ በዮክጭጪ ቀበሌ የሚገኝ ነዉ፡፡ ሀይቁ በተራራ ላይ ከመሆኑ በላይ ክብ ቅርጽ ያለዉ መሆኑና ዙሪያዉ ጥቅጥቅ ባለዉ ድንና በቀርከሃ የተከበበ መሆኑን፤ ክረምት ሆነ…

Read More

የግብርና ሚኒስትር፣ የሰላም ሚኒስትር እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመቶች በምክር ቤት ጸደቀ

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቢኒያም ኤሮ ሹመቶች በምክር ቤት ጸድቀዋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ነው። ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተሾሙት የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ እና የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ ሹመቶችን አፅድቋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን…

Read More

በአረንጓዴ ልምላሜ ያጌጠው – የቤንቾች ቀዬ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የሚገኘው የቤንች ምድር የሰጡትን የሚያበቅል ክረምት ከበጋ የማይጠወልግ ልምላሜን የታደለ ክልል ነው። በቤንች ሸኮ ዞን ባሉ የተለያዩ ወረዳዎች ደን የሚመስልና በመኖሪያ መንደሮች የሚታየው አብዛኛው አረንጓዴ ስፍራ ለምግብነት የሚያገለግሉ ፍራፍሬዎች፣ ቅጠሎችና ስሮችን የያዘ ነው። የቤንቾች ቤት ዙሪያው በአረንጓዴ ተፈጥሮ ያጌጠ ነው። የቤታቸው ሞገስ፤ የምግብ ዋስትናቸውም ጭምር ነው። ከዚህ ከፍ ሲል ደግሞ…

Read More

አመራሩ ተግባራትን በቅንጅነት ለበለጠ ውጤታማነት በመሥራት የሕዝቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ሊደረግ እንደሚገባ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአመራር ቡድን በዳውሮ ዞን የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል ። በክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሠረተ-ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ የተመራው የአመራር ቡድን በዳውሮ ዞን የተቀናጀ የድጋፍ እና ክትትል ሥራዎች እያደረጉ ይገኛሉ። በዚህ ወቅት እንደገለጹት በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የየተቋማቱን ሥራዎች በአግባቡ በመለየት እና…

Read More

የጸረ-ሙስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ ተቋማዊ አደረጃጀትና አሠራር ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዓለም አቀፍ የጸረ-ሙስና ቀን “ትወልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር!” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡ በመድረኩ አጠቃላይ የተቋሙ ሠራተኞች እና አመራር በተገኙበት ለዕለቱ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እና በቀጣይ የጸረ ሙስና ትግሉን ውጤታማ የሚያደርጉ አስተያየቶች ተሰጥበታል፡፡ የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመንግሥት መረጃ ማዕከል አስተዳደር እና ዲጂታል…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ በሆኑት በአቶ ፍቅሬ አማን የተመራው የክልሉ የድጋፍ ቡድን በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ተገኝተው የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ግምገማ ማካሄድ ጀምሯል።

‎የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን በመግብያ እንደገለጹት የክልሉ አስተባባሪ አካላት በሁሉም ዞኖች ላይ በመከፋፈል የድጋፍ ስራ እያካሄደ መሆኑን ጠቅሰው ዓላማው ወቅቱ ትልቅ ትጋት የሚጠይቅ በመሆኑ ሀገራችንን ከሌሎች ሀገር ተርታ እንድትሰለፍ በፓርቲ የሚወርዱ ግቦችን ስኬታማ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል። አክለውም በበጀት ዓመቱ በፓርቲ መሪነት የታቀዱ ተግባራት አፈፃፀማቸውን በመከታተል ጠንካራ ጎኖችን በማስፋትና ጉድለቶችን ለይቶ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሱፐርቪዥን ቡድን በሼይ ቤንች ወረዳ ሲዝ ከተማ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን እያካሄደ ነው

‎የክልሉ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊና የክልሉ ሱፐርቪዥን ቡድን አባል የማታለም ቸኮል (ኢ/ር) ፣ ሌሎች የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳድር አመራሮች በቤንች ሸኮ ዞን ሼይ ቤንች ወረዳ ሲዝ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ምልከታ አድርገዋል። በመስክ ምልከታው በሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቪ እየተሰሩ የእንስሳት እርባታ ማዕከል ሌሎች የልማት ስራዎችን ግብኝተዋል። የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ የማታለም ቸኮል( ኢ/ር)…

Read More

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከልና የህብረተሰቡን ጤንነት ለመጠበቅ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ

‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከዞን ጤና መምሪያ ሀላፊዎች ጋር በወቅታዊ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት እና ቅድመ መከላከል ስራዎች አፈፃፀም ላይ በበይነ መረብ ውይይት አድርጓል። ‎የቢሮው ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደገለጹት የማርበርግ ቫይረስ ስርጭትን በመግታት የህብረተሰቡን ጤንነት ለመጠበቅ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል። ‎ለህብረተሰቡ የማርበርግ ቫይረስ የሚተላለፍበት እና መከላከል በሚቻልበት መንገዶች ላይ ግንዛቤ ለመስጠት በክልሉ ሁሉም…

Read More

በ557 ሚሊዮን ብር በመገንባት ላይ የሚገኘው የጀሙ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ያለበት ደረጃ ተጎበኘ

በምዕራብ ኦሞ ዞን በጀሙ ከተማ በትምህርት ሚኒስቴር በ557 ሚሊዮን ብር በጀት የሚገነባው አዳሪ ትምህርት ቤት ተጎብኝቷል ። በጉብኝቱ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ ጨምሮ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታምሩ ቦኒ ፤ የክልል፣ የዞንና የጀሙ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በቦታው ተገኝተው ጉብኝት አድርጓል። የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስከ ሰኔ 2018…

Read More