ኮሌጁ የህበረሰብ ችግር ሊፈቱ በሚችሉ የስራ ዘርፎች ላይ ባለሙያዎችን በማደራጀት የስራ እድል እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገለጸ።

የታርጫ ፖሊ ቴክንክ ኮሌጅ ላለፉት በርካታ አመታት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማሰልጠን ስራ ፈጣሪ ዜጎች እንዲበራከቱ እየሰራ ይገኛል። የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ኤፍሬም አይሳ ኮሌጁ አሁን ላይ አዲሱን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲን ተግባራዊ በማድረግ በኮሌጁ የሚሰጠውን ስልጠና ያጠናቀቁ ባለሙያዎችን የአከባቢውን ማህበረሰብ ችግር በሚፈቱ ዘርፎች በማደራጀት የስራ እድል እየፈጠረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በኮሌጁ…

Read More

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 48ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመስተዳድር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 48ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል ፡፡ በዚህም መሠረት፦ 1ኛ.በክልሉ በተጨማሪነት እየተሰሩ ያሉ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታ ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ ገምግሟል።በዚህ በተጨማሪነት እየተሰሩ ያሉ አምስት የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በፍጥነት አልቀዉ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆኑ አቅጣጫ አስቀምጧል። 2ኛ. መስተዳድሩ ምክር ቤቱ…

Read More

የአመራር ምዘናው ጠንካራ ተቋም በመገንባት የህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው፦ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአመራር ግምገማና ምዘናው ከብልፅግና ፓርቲ ዕሳቤና መርሆዎች መነሻ ተቋማት የተጣለባቸውን የህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በአመራር መሪነት የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር የሚገመግም እንደኾነ በመድረኩ ተገልጿል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በመድረኩ መክፈቻ ወቅት እንደገለጹት፥ የአመራር ምዘናው ጠንካራ ተቋም በመገንባት የህዝብ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግርኛ ቃለ-መጠይቅ ዋና ዋና ፍሬ-ሐሳቦች

የሰሜኑ ጦርነት መንስኤዎችን በተመለከተ ሕወሓት ከ50 ዓመት በፊት በነበረ ኋላቀር አስተሳሰብ የታሰረ መሆኑና ለውጥን ለመቀበል አለመፈለጉ። ዓለም በቴክኖሎጂና በ”ፕራግማቲዝም” በምትመራበት ዘመን፣ ድርጅቱ በአሮጌው መንገድ ለመጓዝ መሞከሩ ለግጭት ዳርጎታል። ቆሞ ቀሩ ኃይል “ኢትዮጵያ ትፈርሳለች” የሚል የተሳሳተ ስጋት በመዝራት የለውጡን ኃይል እንደ ጠላት ማየቱ። በኢትዮጵያ የነበረው የተሳሳተ ትርክት ዜጎች በጥርጣሬ እንዲኖሩ ማድረጉ። የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ተግባራዊነት በተመለከተ…

Read More

አርሶና አርብቶ አደሮችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ በማድረግ የመሬት አጠቃቀም ሥርዓት እንዲቀየርና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲሻሻል በልዩ ትኩረት መሥራት ያስፈልጋል ፦አቶ ፍቅሬ አማን

የገጠር መሬት ባለይዞታዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ላይ ትኩረት ያደረገ የንቅናቄ መድረክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። መድረኩ ”ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ የይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት’ በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ሲሆን ይህም የክልሉ ግብርና ቢሮ ከኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር በጋራ ትብብር ያዘጋጀው ነዉ። በመድረኩ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለጹት፣…

Read More

የግብርና አገልግሎቶችን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር የአርሶና አርብቶ አደሮች ሁሉዓቀፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያስችላል ፦አቶ ማስረሻ በላቸዉ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የገጠር መሬት ባለይዞታዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ከኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር በጋራ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን ”ዲጂታል ማንነት ለተረጋገጠ የይዞታ ባለቤትነትና ለላቀ የፋይናንስ ተጠቃሚነት’ በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው። በንቅናቄ መድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ…

Read More

ክልላዊ የገጠር መሬት ባለይዞታዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነዉ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ክልላዊ የገጠር መሬት ባለይዞታዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የንቅናቄ መድረኩ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን እና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸዉ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ከኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር በጋራ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን ”ዲጂታል…

Read More

53ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው መደመር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዋጅ ቁጥር 1294/2015 መሠረት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የሚቋቋም ሲሆን በዘርፉ ወጣቶችን ለማሰልጠንና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ምሁራንን ለማፍራት የሚሰራ ነው፡፡ ደንቡ የዩኒቨርሲቲውን ተግባርና ሃላፊነት…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል 13ሺህ 365 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተናን በበይነ መረብ እንደሚፈቱኑ የትምህርት ቢሮ አስታወቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ 184 ትምህርት ቤቶች 13 ሺህ 365 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የብሔራዊ ፈተናቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ዝግጅት እየተጠናከረ መሆኑን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር፣ ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር)ባቀረቡት ሰነድ ገልጸዋል። በክልሉ የተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ እንደተገለጸው፣ ዘንድሮ 15 በመቶ ተወዳዳሪና ብቁ ተማሪዎችን ለማፍራት ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን አጠቃላይ የትምህርት…

Read More

የኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘት የዓድዋ ሰማዕታት ካወረሱን የሉዓላዊነት አደራ የማይነጠል ነው – ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

የኢትዮጵያ ዘላቂና አስተማማኝ የባህር በር ማግኘት የዓድዋ ሰማዕታት ካወረሱን የታሪክና የሉዓላዊነት አደራ የማይነጠል መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ይህን ያሉት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተከበረ በሚገኘው መድረክ ላይ ነው። የዓድዋ ድል ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ጎህ የፈነጠቀና ሰብዓዊ ክብርን ያጎናጸፈ…

Read More