ክልላችን በተጠናከረ የአመራር ቁርጠኝነትና የህብረተሰብ ተሳትፎ አመርቂ ዉጤቶችን እያስመዘገበ ነዉ- አቶ የሺዋስ ዓለሙ

ክልላችን በተጠናከረ የአመራር ቁርጠኝነትና የህብረተሰብ ተሳትፎ አመርቂ ዉጤቶችን እያስመዘገበ ነዉ- አቶ የሺዋስ ዓለሙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በ2018 ዓ/ም የክልሉ መንግስት ስድስት ወራት አፈጻጸም ላይ የሚዲያ መግለጫ ሰጥተዋል። የቢሮው ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፥ በዝግጅት ምዕራፍ ተግባርንና ተልዕኮን መሠረት ያደረገ የአመራር ስምረት በመስጠት እና በጠንካራ የተግባር ቅንጅት ውጤታማ ተግባራትን…

Read More

የወል ትርክት መገንባት ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ ነው

የወል ትርክት መገንባት ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት ወሳኝ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ ገለጹ። በኢትዮጵያ የጋራ ሀገራዊ ትርክቶችን ለመቅረጽ ያለመ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ የወል ትርክት ያሉ ክፍተቶችን የሚያስታርቅ፣በብዝኃነት ውስጥ ያሉ የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የወል ትርክትን መገንባት ለሀገረ መንግሥት…

Read More

ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ የታዳሽ ኃይል አከፋፋይ በመሆን ቀጣናውን አስተሳስራለች – አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር)

በተባበሩት ዐረብ ኢምሬት አቡዳቢ ከጥር 03 እስከ ጥር 04 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ “Powering Humanity: Renewable Energy for Shared Prosperity” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው 16ኛው የዓለም አቀፉ የታዳሽ ኃይል ኤጀንሲ (IRENA) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በቋሚ መልዕክተኛዋ አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ተወክላ በመሳተፍ ላይ ትገኛለች። አምባሳደር ጀማል በጉባኤው ባቀረቡት የኢትዮጵያ ብሔራዊ መግለጫ፥ ሀገሪቱ የምትጠቀመው…

Read More

የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል በድምቀት መከበር ጀምሯል።

የቤንች ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ ቢስት ባር በሲዝ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ባህላዊ ሁነቶች መከበር ጀምሯል። ከቢስት ባር ሁነቶች መካከል አንዱ የሆነው የፖሊስ ማርሽ ባንድ የአደባባይ ትዕይንት አካሂደዋል። የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ “ቢስት ባር” ለማክበረ የተለያዩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ፣ የብሔረሰቡ ተወላጆችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች መከበር መጀመሩን የቤንች ሸኮ ዞን…

Read More

በአፍሪካ የውሃ ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ይጀመራል

በአፍሪካ የውሃ ደህንነት ላይ ትኩረቱን ያደረገው 51ኛው የአፍሪካ ሕብረት የቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ (PRC) መደበኛ ስብሰባ ከዛሬ ጀምሮ የህብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችው አዲስ አበባ መካሄድ ይጀምራል። ስብሰባው”ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” በሚል የአፍሪካ ህብረት ባዘጋጀው የ2026 መሪ ሃሳብ የሚደረግ ነው። የዘንድሮው መሪ ሀሳብ ጭብጥ በአፍሪካ የውሃ ደህንነትና ንጽህና…

Read More

“ባለፉት ስድስት ወራት ባከናወናቸው የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ስራዎች ወደ ላቀ ምዕራፍ የተሸጋገሩ ውጤቶች ተመዝገበዋል።” ሰማ ጥሩነህ (ዶ.ር)

የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ በ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ በባህርዳር ከተማ ሲያካሂድ የነበረው መድረክ ተጠናቀቀ። በግምገማ መድረኩ የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2018 ዓ.ም የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በውይይቱም የተገኙት የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ…

Read More

“ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር የኢትዮጵያና ህዝቦቿን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራል።አቶ ፍቃዱ ተሰማ

“ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ” በሚል መሪ ሀሳብ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ሲካሄድ የነበረዉ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተጠናቋል። የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የፓርቲው ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር ፍቃዱ ተሰማ እንደተናገሩት ያለፉት ስድስት ወራቶች ይህን ግዙፍ ፓርቲ የሚመጥን ጠንካራ አደረጃጀት ለመገንባት አደረጃጀቶችን…

Read More

ለምርጫ ሂደቶች ውጤታማነት የተናበበና የተቀናጀ የሚዲያ ኮሚዩኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት ስራ ያስፈልጋል – ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር)

የብልፅግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሲያካሂድ የነበረውን የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ አጠናቋል። በማጠቃለያ መድረኩ የብልፅግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) እንደገለፁት የፓርቲውን ዕሳቤዎች፤ ያስመዘገባቸውን ድሎች እንዲሁም ትልሞች ሁሉንም የሚዲያና የኮሚኒኬሽን አማራጮች በመጠቀም ለህዝብ የማሳወቅና ግንዛቤ የመፍጠር ተግባራት በላቀ ሁኔታ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል። በቅድመ…

Read More

ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የደካ ዳሩ ሰላም መስጊድ ተመረቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ካፋ ዞን ደካ ከተማ ውስጥ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ሙሉ ተሳትፎ ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የዳሩ ሰላም መስጊድ በደማቅ ስነ-ስርዓት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። በ1,950 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው ይህ ዘመናዊ መስጊድ፣ ለከተማው ተጨማሪ ውበትና ቅርስ ከመሆኑም ባሻገር፣ የማህበረሰቡን የመተባበርና የአንድነት መንፈስ በተግባር ያሳየ ፕሮጀክት መሆኑ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ…

Read More