በማህበራዊ ዘርፍ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2018 በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በቦንጋና ታርጫ የሳተላይት ደም ባንኮች ደም ለማሰባሰብና ለማሰራጨት 3 ሺህ 450 ዩኒት ለማሰባሰብ ታቅዶ 82 በመቶ መፈፀም መቻሉንና በወባ በሽታ የመያዝ ምጣኔን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነፃፀር በ29.5 መቀነስ መቻሉም በሪፖርቱ…

Read More

የፍትህና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለይቶ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት መሰራቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ገለጸ

‎የክልሉ የመንግስት የስድስት ወራት አፈፃፀም ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት በቦንጋ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል። ‎በመድረኩ የክልሉን ዋና ዋና የመንግስት አፈፃፀም የስድስት ወር ሪፖርት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ የፍትህ ዘርፉን ማዘመንና ተደራሺነትን ማስፋፋት በመንግሥት በልዩ ትኩረት ከሚፈፀሙ ተግባራት አንዱ መሆኑን ገልፀዋል። ‎ነፃና ገልለተኛ የፍትህ ተቋማትን ለመገንባት የተወሰደው እርምጃ ውጤት…

Read More

የዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ ወደ ብልጽግና የምታደርገው ጉዞ አንድ እጥፋት ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ ወደ ዘመናዊነት እና ብልጽግና የምታደርገው ጉዞ አንድ እጥፋት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ሥራን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት ነው፡፡ ኢትዮጵያ እምቅ አቅሟን እና ታላቅ ርዕይዋን የሚመጥን ሌላ ተጨማሪ ሜጋ ፕሮጀክት ጀምራለች። የቢሾፍቱ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት…

Read More

በመንግሥት በህብረተሰና በባለድርሻ አካላት የጋራ ተሳትፎ በክልሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች እየተጠናከረ ይገኛል ። ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ

‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፓርቲና የመንግስት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። ‎በክልሉ በስድስት ወራት ውስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና የመንግስት አፈፃፀሞችን ሪፖርት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ በመንግሥት በአጋር አካላት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የመንገድ የውሃና የመስኖ መሰረተ ልማቶች ተጠናክሮ እየተሰሩ እንደሆነ ገልፀዋል። ‎በህብረተሰቡ ለመሰረተ ልማት ግንባታ በገንዘብ በጉልበትና…

Read More

ባለፉት ስድስት ወራት በኢኮኖሚ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች ተጠናክረው ሊቀጥል እንደሚገባ የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ አስታወቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለፉት ስድስት ወራት በኢኮኖሚ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች ተጠናክረው የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2018 በጀት የግማሽ ዓመት የፓርቲና የመንግስት ተግባራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ እንደገለጹት በኢኮኖሚ…

Read More

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለቀጣናዊ ትብብር እና የኃይል ትስስር ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በራስ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን የመገንባት ተምሌት ከመሆን ባለፈ ለቀጣናዊ ትብብር እና የኃይል ትስስር ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድና በይቻላል መንፈስ እውን መሆኑ ይታወቃል። ይህም ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ጎረቤት ሀገሮችን ጭምር በኃይል አቅርቦት ተደራሽ በማድረግ ለአፍሪካ አንድነትና ትስስር ያላትን ሚና…

Read More

በወልደሃኔ – ዱርጊ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ንጣፍ ለመጀመር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ በመከናወን ላይ ነው

የማዕከላዊ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎችን በሚያገናኘው የወልደሃኔ – ዱርጊ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ንጣፍ ለመጀመር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ በመከናወን ላይ ነው። የመንገድ ግንባታው በዳውሮ ዞን እና በጠምባሮ ልዩ ወረዳ በኩል በሁለት አቅጣጫ በመከናወን ላይ ሲኾን፥ አጠቃላይ 41 ኪሎሜትር ይሸፍናል። አሁን ላይ የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ በጠምባሮ በኩል ያለውን የፕሮጀክት ክፍል…

Read More

ሀገራዊ ምርጫ የተሳካ እንዲሆን የህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሚና የላቀ ነው- ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)

የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የዋና ጽ/ቤት እና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች አመራሮች በተገኙበት በአዲስአበባ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያ ከወራት በኋላ የምታካሂደው 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ነፃና ተምሳሌታዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የላቀ…

Read More

የሸበሌ ሪዞርት ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጠናቀቀ

የፌዴራል መስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር እና የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ ከሶማሊ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አህመድ ሹክሪና ከሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን የተጠናቀቁ የፕሮጀክት ሥራዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ኃላፊዎቹ በጉብኝታቸው ወቅት የሸበሌ ሪዞርት ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ መጠናቀቁን ያረጋገጡ ሲሆን፣ ለምረቃ ሥነ ሥርዓት እየተደረገ ያለውን ዝግጅትም ተመልክተዋል። በተጨማሪም፣ በፕሮጀክቱ ግንባታ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የኢትዮጰያን ፈጣን የአየር ትራንስፖርት እድገት እና እየሰፋ የመጣውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለምአቀፍ ትስስር ዘላቂ ለማድረግ ወደ 25 ሚሊዮን የሚጠጉ መንገደኞችን በአመት የማስተናገድ አቅሙ ላይ ከደረሰው ከአዲስ አበባ ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተጨማሪ አዲስ ሜጋ ጣቢያ እየለማ ይገኛል። ይኽ የተለያዩ አውሮፕላን ማረፊያዎችን የመገንባት ስትራቴጂ ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግምባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ አላማን ያነገበ ነው።…

Read More