ለፖሊስ መኮንኖች የሚሰጠው የማዕረግ ሽግግር የደረጃ ዕድገት ብቻም ሳይሆን ሀገራዊና ክልላዊ አደራም ጭምር ነው፦ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን በሞዲዮ ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም ለሶስተኛ ጊዜ ያሰለጠናቸው የመካከለኛ እና ከፍተኛ ማዕረግ ሽግግር ሰልጣኝ የፖሊስ መኮንኖችን አስመረቀ። ተመራቂዎቹ የቆይታ ጊዜያቸዉን የሸፈኑ ከዋና ሳጅን ወደ ረዳት ኢንስፔክተር እና ከኢንስፔክተር ወደ ዋና ኢንስፔክተር ሽግግር የሚያደርጉ ናቸው። በምረቃው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለጹት ፤ የፖሊስ ሠራዊትና የጸጥታ መዋቅር ዋነኛ…
