Getenesh Gebeyehu

በህብረተሰቡ ሲነሱ ለነበሩ የልማት ጥያቄዎች መንግሥት የሰጠው ምላሽ የሚደነቅ መሆኑን የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ

በዳውሮ ዞን ለረዥም ዓመታት የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበረው የወልደሀነ-ዱርጊ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ መጀመር እንዲሁም የታርጫ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቀው ለአግልግሎት መብቃቱ እንዳስደሰታቸው ያነጋገርናቸው የአከባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ። በዳውሮ ዞን የገና እና የዛባ ወረዳዎች ከአጎራባች የካምባታ እና ጣምባሮ አከባቢዎች ጋር ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ጠንካራ ማህበራዊና ኢኮኖሚ ትስስር እንዳላቸው ያነሱት የአከባቢው ነዋሪ ከሆኑት…

Read More

ኢትዮጵያ በዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው

ኢትዮጵያ “ደህንነቱ ለተጠበቀ ነገ ዓለም አቀፍ የፖሊስ ኃይል ትብብር” በሚል መሪ ሀሳብ በዱባይ እየተካሄደ ባለው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው። በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የተመራው ልዑክ በፈረንጆቹ ከመጋቢት 5 እስከ 7 ቀን 2024 በዱባይ እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ልዑካን ቡድኑ በቦታው ሲደርስ በዱባይና ሰሜን ኤምሬቶች የኢፌዲሪ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የታርጫ ከተማ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት መርቀው ከፈቱ።

ከ230 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ውጪ የተገነባው የታርጫ ከተማ የንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ እና ሌሎች የክልልና የፌዴራል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተኙበት ተመርቋል። ከተለያዩ ረጂ ተቋማት በተገኘው 170 ሚሊዮን ብር እና 1.142 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገነባው የውሃ…

Read More

በርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ ዳውሮ ዞን ገባ

በልዑኩ የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ይገኙበታል። የሥራ ኃላፊዎቹ ታርጫ ከተማ ሲደርሱ የከተማው ነዋሪዎች፣ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ልዑካኑ በዳውሮ ዞን በሚኖራቸው ቆይታ በቀጣዮቹ ቀናት የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውሮ እንደሚጎበኙና የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን እንደሚያስመርቁ ይጠበቃል። በዕድገቱ በዛብህ

Read More

የተቋም ግንባታ ውጥናችን ስኬታማነቱ የሚረጋገጠው በጠንካራ ሴቶች ወሳኝ ተሳትፎ ነው ፡- ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ::

የተቋም ግንባታ ውጥናችን ስኬታማነቱ የሚረጋገጠው በጠንካራ ሴት የሰራዊት አባላት ወሳኝ ተሳትፎ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ፡፡ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን “የሴቶች ተጋድሎ ለሰላም እና ለፍትሕ” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ መርሐ ግብሮች ተከብሯል። ሌ/ጀ ይልማ መርዳሳ በዚህ ወቅት÷ በዓድዋ አርበኛዋ እቴጌ ጣይቱ፣ በሴት አውሮፕላን አብራሪዋ ሙሉ እመቤትና በሌሎች ሴት…

Read More

የኢትዮጵያ አየር መንገድና የቦይንግ ትብብር የኢትዮጵያና የአሜሪካንን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ያጠናክራል – አምባሳደር ኧርቪን ሆሴ ማሲንጋ::

የኢትዮጵያ አየር መንገድና ቦይንግ የደረሱበት የትብብር ደረጃ የኢትዮጵያና የአሜሪካንን ምጣኔ ኃብታዊ ግንኙነት ለማጠናከር ትልት አስተዋጽኦ ያደርጋል ሲሉ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ሆሴ ማሲንጋ ገለጹ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአፍሪካ በዓይነታቸው የመጀመሪያ የሆኑ 20 ቦይንግ 777 ኤክስ 9 የተሰኙ ግዙፍ አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግ ኩባንያ ጋር በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሥምምነት አድርጓል። በመርኃ-ግብሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ…

Read More

በክልሉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመከላከያ እና ለመቆጣጠር የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መስራት እንሚጠበቅ ተጠቆመ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ ዳይሬክቶሬት የሲ.ዲ.ሲ ፕሮጀክት የግማሽ ዓመት አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በክልሉ ቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም ባለፉት 6 ወራት ኤች አይ ቪ ኤድስ ከመከላከያ እና ከመቆጣጠር አንፃር በርካታ ውጤታማ ተግባራት የተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረው በዚህ…

Read More

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 በተለያዩ ፕሮግራሞች በቦንጋ ከተማ ተከብሯል::

ማርች 8 ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም ለ133ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ48ኛ ጊዜ በክልላችን ደግሞ ለ3ኛ ጊዜ በተለያዩ መርሃግብሮች ተከብሯል። ዕለቱን በማስመልከት ንግግር ያደረጉት በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሴቶች ሊግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ውባለም በዛብህ በፈረንጆች አቆጣጠር በ1990ዎቹ ተንሰራፍቶ የነበረው ግፍ፣ጭቆናና በደል በሴቶች ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ ንቅናቄ እንዲያደርጉ መንስኤ መሆኑን ተናግረዋል ። በዚህም ከ15 ሺህ…

Read More

በዋና ዋና ማክሮ ኢኮኖሚ ዘርፎች የተመዘገበው አፈጻጸም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ7 ነጥብ 9 በመቶ እንደሚያድግ አመላካች መሆኑ ተገለፀ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2016 የሁለተኛው ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ማካሄድ ጀምሯል። በመድረኩም ያለፉት ስድስት ወራት የኢኮኖሚ ማህበራዊ እንዲሁም የፍትህና አስተዳደር ዘርፍ አፈጻጸም ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፤ የኢኮኖሚ ዘርፍ አፈጻጸምን ባቀረቡበት ውቅት ኢትዮጵያ በ2015 የ7 ነጥብ 2 በመቶ እድገት ማስመዝገቧን አስታውሰዋል። በተያዘው በጀት…

Read More

በዓለም አቀፉ የወጣቶች ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እየተሳተፉ ነው::

በሩሲያ ሶቺ ከተማ እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የወጣቶች ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያውያን እየተሳተፉ ይገኛል። በፌስቲቫሉ ላይ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡ ከ20ሺህ በላይ ወጣቶች እየተሳተፋ ይገኛል። በዚህ ፌስቲቫል ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም እየተሳተፋ ሲሆን÷ መድረኩ ወጣቶች ሀገራቸውን እንዲያስተዋውቁ እና እርስ በእርስ ልምድና ተሞክሯቸውን እንዲለዋወጡ የበኩሉን እገዛ እንደሚያደርግ መገለፁን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡ ከፌስቲቫሉ ጎን ለጎን የባህል፣ የስፖርት፣…

Read More