Trendings

BLOGS

የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በመሬት ናዳና መንሸራተት ለተፈናቀሉ ወገኖች ግምቱ ግማሽ ሚሊየን ብር የሚያወጣ የምግብ እህሎች ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉ በካፋ ዞንና በቤንች ሸኮ ዞን በመሬት መንሸራተት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች እንደሚሰጥም ታውቋል። የሰብዓዊ ድጋፉን ይዘው የቀረቡት የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ በላይ አሪሶ እንደተናገሩት ግምታቸው ግማሽ ሚሊዮን የሚያወጡ የምግብ እህሎችን ለተጎጂዎች ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ። ከአቅም በላይ በሆነ የተፈጥሮ አደጋ በመሬት መንሸራተት ሳቢያ የተፈናቀሉ ወገኖችን ባሉበት አካባቢ ቀርቦ በማጽናናት ሰብዓዊነታታቸውን…

Read More

እየጣለ ያለውን ከፍተኛ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት የተዘጋውን መንገድ ጊዜያዊ ጥገና እያደረ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ገለጸ

በቤንች ሸኮ ዞን ከዋቻ ማጂ ወደ ሼይቤንች የሚወስደው መንገድ በመዘጋቱ በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ በተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንሸራተቶች እየተከሰቱ ይገኛሉ ፡፡ በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ ቃሻ ቀበሌ ላይ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት ዜጎች እንዲፈናቀሉ ከማድረጉም በላይ በቤንች ሸኮና በምዕራብ ኦሞ…

Read More

በኦሊምፒክ ጨዋታዎች ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ብሔራዊ የጀግና አቀባበል ይደረግለታል – የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር

በፓሪስ በተካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ብሔራዊ የጀግና አቀባበል እንደሚደረግለት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶች በውድድሩ የሚገባውን ተጋድሎ መፈጸማቸውን ገልጿል። ሚኒስቴሩ የኢትዮጵያን የኦሊምፒክ ተሳትፎ በማስመልከት መግለጫ አውጥቷል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1956 በሜልቦርን በተካሄደው 16ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች አንስቶ በአጠቃላይ 15 ጊዜ ተሳትፎ ማድረጓን ገልጿል። ከሜልቦርኑ በስተቀር ከኦሎምፒክ በ14ቱ የተሳትፎ መድረኮች ካለ ሜዳሊያ ተመልሳ አታውቅም…

Read More

ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን ለማሳደግ ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር እንደምትሰራ ገለጸች

ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር ኢኮኖሚዋን ለማሳደግ እንደምትሰራ በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ኡሪያት ቻም ኡጋላ ገለጹ፡፡ በአምባሳደሩ ከቲቪ ብሪክስ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፥ የኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀል ስላለው ጥቅምና ተያያዥ ጉዳዮች አንስተው አብራርተዋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ከአሁን በፊት በተለያዩ ባለብዙ ወገን ግንኙነት ተሳትፎ እንደነበራትና እንዳላት አንስተው፤ ከዚህም መካከል አንዱ ብሪክስን መቀላቀሏ እንደሆነ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከብሪክስ ሀገራት ጋር ያላት…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በህገ-ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ የመውሰድ ተግባር

መንግሥት የተለያዩ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስራዎችን በመስራት በቅርቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ይፋ አድርጓል። ይህ አዲሱ የኢኮኖሚ ማሻሻያ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትና ዘላቂነትን በመደገፍ ዘመናዊና ጤናማ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማእቀፍ ለመመሥረት የሚያስችል ነው። የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ፈጠራን የሚያበረታታና ምቹ የኢንቨስትመንትና የንግድ ዘርፍ ከባቢና ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል። የሀገር ውስጥ ምርትና ምርታማነት አቅምን የሚያጠናክርና ጥራት ያለው አገልግሎትን በብቃት…

Read More

2016 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ዕድገት ያስቀጠልንበት ዓመት ነው -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

2016 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ዕድገት ያስቀጠልንበት ዓመት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ተጠሪነታቸው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆኑ አስፈጻሚ ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2017 ዕቅድ የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተጠናቀቀው በጀት ዓመት በብዙ መልኩ ስኬት የተመዘገበበት ነበር ብለዋል። በዚህም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ እድገት ማስቀጠል ተችሏል ነው ያሉት። ለሰላም…

Read More

በካፋ ዞን፣ ጊምቦ ወረዳ የተከሰተውን ወቅታዊ የሠላም መደፍረስ ለመፍታት ያለመ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ካፋ ዞን፣ ጊምቦ ወረዳ፣ ሾምባ ኪጭብ ቀበሌ የተከሰተውን ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ለመፍታት ያለመ ህዝባዊ ውይይት በቀበሌው ተካሂዷል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዲሁም የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ ከሌሎች የክልል እና የካፋ ዞን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ከአከባቢው ከተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ወይይት አድርገዋል።…

Read More

“በጎነት ለጤንነት” በሚል መሪ ቃል የ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ነፃ የህክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም በካፋ ዞን ገብረ ፃዲቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል ተካሂዷል።

የ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራሙን የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እና የካፋ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አክሊሉ አሰፋ በይፋ አስጀምሯል። የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንዳሉት” በጎነት ለጤንነት” በሚል መሪ ቃል ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የነፃ ምርመራና ህክምና…

Read More

ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ የካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫን በጋራ ለማክበር በተደረገው ንቅናቄ ተሰብስቧል፦ የካፋ ዞን አስተዳደር

የዘንድሮውን የካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫ በጋራ ለማክበር እየተደረገ ባለዉ የገቢ አሰባሰብ በእስካሁኑ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የካፋ ዞን አስተዳደር ገለጸ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በቀደምት አባቶች ገለዜ አንስቶ በየዓመቱ እየተከበረ ለብዙ ዘመናት የቆየውን የካፌቾ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል ለማክበር የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነዉ ብለዋል። በበዓሉ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የብሔሩ ተወላጆች…

Read More

በሐምሌ ወር የሰለጠነ የሰው ሃይል ወደ አውሮፓ ሀገራት መላክ ተጀምሯል፦ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል

በሐምሌ ወር የሰለጠነ የሰው ሃይል ወደ አውሮፓ ሀገራት መላክ መጀመሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ፡፡ ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ፤ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዕቅድ አፈፃፀም ተገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫዎች መቀመጣቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተገኙ ልምዶችን በመውሰድ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሁሉም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት የራሳቸውን ሚና በአግባቡ በመለየትና…

Read More