በኦሊምፒክ ጨዋታዎች ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ብሔራዊ የጀግና አቀባበል ይደረግለታል – የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
በፓሪስ በተካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ብሔራዊ የጀግና አቀባበል እንደሚደረግለት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ። አትሌቶች በውድድሩ የሚገባውን ተጋድሎ መፈጸማቸውን ገልጿል። ሚኒስቴሩ የኢትዮጵያን የኦሊምፒክ ተሳትፎ በማስመልከት መግለጫ አውጥቷል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1956 በሜልቦርን በተካሄደው 16ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች አንስቶ በአጠቃላይ 15 ጊዜ ተሳትፎ ማድረጓን ገልጿል። ከሜልቦርኑ በስተቀር ከኦሎምፒክ በ14ቱ የተሳትፎ መድረኮች ካለ ሜዳሊያ ተመልሳ አታውቅም…
