ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል
ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት የቴክኒክና ሙያ የአሰልጣኝ መምህራን አቅም ግንባታ ላይ ትኩረት መደረጉን የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። ሚኒስቴሩ ከነገ ጀምሮ “ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ኃሳብ ለ12 ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እንደሚያስጀምር አስታውቋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ ሥልጠናው አዲስ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ ወደ ሥራ መግባቱን መሠረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን…
