ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ የሚያቋቁሙት የኮሪደር አስተዳደር የወደብና የትራንስፖርት አገልግሎት ቀልጣፋ እንዲሆን ያስችላል ተባለ
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እንደገለጹት÷ በጅቡቲ ወደብ ላይ የአሰራር አለመቀላጠፍ ከገጠመ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንትና ተወዳዳሪነት ላይ ትልቅ ተጽእኖ ይኖረዋል። ወደ ሀገር የሚገቡና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች በጅቡቲ ወደብ በኩል እንደሚተላለፉ ጠቅሰው፤ የወደብ አገልግሎቱ ቀልጣፋ ካልሆነ ምርቶች በውጭ ገበያ የመወዳደር ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የወጪ እና ገቢ ንግዱን እንዲሁም በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መካከል…
