Trendings

የ2018 በጀት ዓመት የደረጃ ‘ሐ’፣’ለ’ እና ‘ሀ’ ግብር ከፋዮች የግብር ማስጀመሪያ ክልላዊ ንቅናቄ እየተካሄደ ነዉ

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ) በተገኙበት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የደረጃ ‘ሐ’፣’ለ’ እና ‘ሀ’ ግብር ከፋዮች የግብር ማስጀመሪያ ክልላዊ ንቅናቄ መድረክ በሚዛን አማን ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። ክልላዊ የንቅናቄ መድረኩ ”ለክልላችን ልማት ግብርን በታማኝነት በሚል መርሕ ቃል ነዉ እየተካሄደ የሚገኘዉ። በመድረኩ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ…

Read More

የመንግስትን የ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀንም በተመለከተ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች ዶ/ር ዐብይ አህመድ ከሰጡት ማብራሪያ :-

በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ይህ ዓመት የኢትዮጵያ ማንሰራራት እንደሚሆን መናገሬ ይቃወሳል ። የለውጥ ማፅናት ተጠናቆ የሪፎርሙን ውጤት ማየት የቻልንበት ዓመት ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ ታይተው ያልታወቁ ታላላቅ ድሎችን የተጎናፀፍንበት ዘመን ነው፡፡ የፓርላማ አባላት ክትትል እና ድጋፍን በማጠናከር ላደረጉት ጉልህ ተሳትፎ ምስጋና ይገባቸዋል።

Read More

የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን ኑሮ የሚቀይሩ እና ተጠቃሚነታቸውን በተጨባጭ የሚያረጋግጡ ዜጋ ተኮር ሥራዎች በመሆናቸው ተጠናክሮ ይቀጥላሉ፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ”በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ 4! በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ክልላዊ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። በብልጽግና ፓርቲ መሪነት ባለፉት ዓመታት ጀምሮ እየተከናወኑ የሚገኙ የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን ኑሮ የሚቀይሩ እና ተጠቃሚነታቸውን በተጨባጭ የሚያረጋግጡ ዜጋ…

Read More

በክልሉ የተጀመረውን ተስፋ ሰጪ የግብርና ልማት እንቅስቃሴን ወደ ላቀ ምዕራፍ ማሻገር ከባለድርሻ አካላት የሚጠበቅ ኃላፊነት መሆኑን የግብርና ቢሮ አስታወቀ ።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ልማት አጋር አካላት ግንኙነት አማካሪ ካውንስል የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተደረገ ነው። በምክክር መድረኩ የተገኙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የግብርና ልማት ዕድገትን በማፋጠን የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬታማ ተግባራትን ለማጠናከር የምርታማነት ዕድገት ማነቆ የሆኑ መሠረታዊ ችግሮችን ለይቶ እየፈቱ መሄድ ይገባል ብለዋል።…

Read More

የጥናትና ምርምር ሥራዎች በትምህርት ጥራት ላይ ትኩረት ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ

ቦንጋ የትምህርት ኮሌጅ ዓመታዊ የምርምር ጉባኤ “በጥናት የተደገፈ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ” በሚል ጭብጥ እያካሄደ ነው። በጉባኤው በተለያዩ ትምህርት እና ማህበረሰብ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረጉ 30 የምርምር ውጤቶች እንደሚቀርቡ ማወቅ ተችሏል። ጉባኤውን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዱባሌ ሳህሌ:-የጋራ ጥረታችንን ወደፊት የሚያሻግረውን የኢኖቬሽን፣ የትብብርና ትስስር ጉባኤ በማዘጋጀታችን በኮሌጁ ማህበረሰብ ስም ኩራት ይሰማኛል…

Read More

መንግስት ለዜጎች ምቹና ተስማሚ አካባቢ ለመፍጠር እና የዜጎችን ህይወት ለመቀየር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል:-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በቦንጋ ከተማ “ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድረግ ” በሚል መሪ ቃል ክልል አቀፍ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ እየተካሄደ ነው ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንዳሉት፣መንግስት ለዜጎች ምቹና ተስማሚ አካባቢ ለመፍጠር እና የዜጎችን ህይወት ለመቀየር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ክልሉ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና እንክብካቤ እንደሚታወቅ ጠቅሰው አሁን በ”ጽዱ…

Read More

የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ከጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጎን ለጎን አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ አከናወኑ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በቦንጋ ከተማ “ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድረግ ” በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው ዙር ክልል አቀፍ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ዘመቻ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና የኢፌደሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሚ በጋራ በመሆን አስጀምረዋል። የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ”ከጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ጎን ጎን በቦንጋ ከተማ…

Read More

“ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድረግ ” በሚል መሪ ሃሳብ ሁለተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ዘመቻ ተጀመረ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በቦንጋ ከተማ “ጽዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድረግ ” በሚል መሪ ቃል ክልል አቀፍ የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ዘመቻ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል። መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና የኢፌዲሪ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሚ በጋራ በመሆን ነው ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ባደረጉት ንግግር የአካባቢያችን…

Read More

ክልላዊ የበጀት ድልድሉ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ በሚያስችል መልኩ ተግባራዊ መደረግ አለበት። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2018 በጀት ዓመት ክልላዊ የበጀት ድልድልና የገቢ እቅድ ላይ የባለድርሻ አካላት ምክክር በቦንጋ ከተማ እየካሄደ ይገኛል። በምክክር መድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ ከዚህ ቀደም ሲተገበር የነበረው ክልላዊ የበጀት ቀመርና ድልድል ለክልል ማዕከል የካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ አነስተኛ ሚና የነበረው በመሆኑ በቀጣይ ይህንን አሰራር በማሻሻል የ2018 በጀት…

Read More

የወባ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር ስራ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ ይጠይቃል ተባለ

የሸካ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ተግባር ያለበት ደረጃና የቀጣይ ተግባራት ዕቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቴፒ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የውይይት መድረኩን የመሩት የሸካ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ በላቸው ጋራ እንደተናገሩት የወባ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር ስራ የሁሉንም ህብረተሰብ ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል። በየደረጃው የሚገኘው የፓርቲና የመንግስት አመራር…

Read More