በክልሉ ግብርና ቢሮ በዘላቂ የመሬት አያያዝ ፕሮግራም አበረታች ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመላከተ።
ከኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ የተወጣጣ ቡድን በክልሉ በዘላቂ የመሬት አያያዝ ፕሮግራም እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ አድርገዋል። ቡድኑ፥ በዳዉሮ ዞን በኢሠራ ወረዳ በጉዛ፣በጉይቲ እና ከጉድሙ ቀበሌዎች በዘላቂ መሬት አያያዝ ፕሮግራም የተሠሩ የአፈና ውሃ ጥበቃ፣ የስነ-አካላዊና ስነ-ህይወታዊ ስራዎች እንዲሁም በፕሮግራሙ የኑሮ ማሻሻያ ማዕቀፍ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ተዘዋውረው ጎብኝቷል።…
