በሸካ ዞን ግብርናን ለማዘመን የሚያስችሉ የ117 ሚሊዮን ብር የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉና ከ117 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቁ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል። በክልሉ የግብርና ቢሮ በምግብ ስርዓተ ማጠናከሪያ ፕሮግራም ድጋፍ የሚገነቡትን የእነዚህን ፕሮጀክቶች መሠረተ ድንጋይ ያስቀመጡት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ናቸው። በዞኑ ያለውን እምቅ የግብርና አቅም ወደ ተሻለ ደረጃ…
