በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አስተዳደር የታርጫ ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በመሆኑ መደሰታቸውን የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የተሽከርካሪ ባለንብረቶች በበኩላቸው መናኸሪያው ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ንብረት ውጭ በሚያድርበት ወቅት ካለው ስጋት ነፃ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች አቶ ወ/ማርያም ብትሬ እና ወ/ሮ አባይነሽ ሳና ቀደም ሲል የታርጫ ከተማ መናኸራያ የመንገደኞች ማረፍያ፣ ካፍቴሪያ፣ የትኬት መቁረጫ ቢሮና መኪና ማቆሚያ ቦታ ምቹ ያለመሆኑን አንስተው አሁን ግን ዘመናዊ መናኸሪያ ተገንቢቶ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል። በግንባታ ምክንያት…

Read More

የክልሉ መንግስት የህዝብን ጥያቄ ለመመለስ በሚያስችሉ የልማት ስራዎችን በትኩረት ይሰራል፦ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

በምረቃ ስነስርዓት ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የለውጡ መንግስት በርካታ የተወዛዘፉ የቤት ስራዎችን ተቀብሎ ሲሰራ መቆየቱን አንስተው ዛሬ የተመረቀው የታርጫ ህዝብ ትራንስፖርት መናኸሪያ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የመነኸሪያ ያለመኖር ለዜጎች ለስምርት ምቹነት፤ የተሸከርካሪ ብቃት ለማረጋገጥ ፣ ተሳፋሪውን ተገቢውን ታርፍ ለማስከፈል ማነቆ ከመሆኑም ባሻገር ህዝብን ለእንግልት እያዳረገ መቆየቱን ተናግረው፤ አሁን የግንባታው መጠናቀቅ…

Read More

የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በማዳመጥና ምላሽ በመሰጠት እየተሰሩ ያሉት ተግባራት ተጠናክሮ ይቀጥላል :- አቶ ፍቅሬ አማን

በከተሞች የህዝብ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለማዳመጥና ደረጃ በደረጃ ለመፍታት የሚያስችል የህዝብ ውይይት መድረክን አስመልክቶ ክልላዊ የዘርፍ አመራሮች ውይይት መድረክ የክልል የሚመለከታቸው ተቋማት አመራሮችና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በተገኙበት በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ባለፉት ዓመታት ከከተማ ነዋሪዎች ጋር በተደረጉት ህዝባዊ የውይይት መድኮች የተነሱትን መሰረታዊ የልማትና…

Read More

መንግስት የዜጎችን ህይወት ትርጉም ባለው ሁኔታ በሚቀይሩ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ፦ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ማሪ ማንሳ ወረዳ የተገነባውን የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከልና በወረዳው የተገነባውን የአስተዳደር ህንፃ መርቀው ከፍተዋል። በማሪ ማንሳ ወረዳ ማሪ ከተማ የተገነባው የቁም እንስሳት የግብይት ማዕከል በአካባቢው ካለው የእንስሳት ዕምቅ ሀብት የሚመነጨውን ኢኮኖሚ በአግባቡ ለመጠቀም የሚያግዝ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል። አካባቢው በእንስሳት ሀብት፣ በእርሻና…

Read More

ተጠናቅቆ ለአገልግሎት የበቁና ቀጣይ የሚገነቡ ፕሮጀክቶች የብልጽግና ፓርቲ ለህዝብ ጥያቄ የሰጠዉ ምላሽ ማሳያ ናቸዉ፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የህዝብን የልማት ጥያቄ በተገቢው መንገድ ለመመለስ በክልሉ መንግስት የተጀመሩ የተለያዩ ልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን የገለጹት በዳውሮ ዞን ኢሳራ ባሌ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ባኖሩበትና ግንባታው የተጠናቀቀውን የተለያዩ የልማት ስራዎችን መርቀው በከፈቱበት ወቅት ነው። ባለፉት ዓመታት የተሰጡ የቤት ስራዎች ተጠናቅቆ እየተመረቁ መሆኑን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ የተጀመሩ…

Read More

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ግንባታና የአፍሪካ አቪየሽን ልህቀት ተምሳሌት ነው – ከፍተኛ አመራሮች

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ግንባታ ጉልህ ሚናው ብሔራዊ ኩራትን ከመፍጠር ባለፈ የአፍሪካ አቪየሽን የልህቀት ተምሳሌት ነው አሉ የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት በማስመልከት ከደንበኞችና አጋሮች ጋር የደንበኞች ተሞክሮ መድረክ እየተካሄደ ነው። በመርሐ ግብሩ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ(ዶ/ር)፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው…

Read More

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሰራ ወረዳና ባሌ ከተማ አስተዳደር የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎች መርቀው ከፍተዋል።

ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ በኢሰራ ባሌ ከተማ አስተዳደር ከ12.3 ሚለየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባውን የኢሰራ ባሌ ከተማ ሞዴል ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፍተዋል። ይህ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንሸቲቭ የሆነው ቅድሜ ሞዴል ትምህርት ቤት የትምህርት ጥራት ችግር በመፍታት፤ ስብራትን ለመጠገን በክልሉ በዘርፉ እየተከናወኑ ካሉት ዘርፌ ብዙ ተግባራት አንዱ መሆኑ ተገልጿል። በተያያዘው ዜና በክልሉ መንገድ ልማትና…

Read More

የብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚያደርገውን የይምረጡኝ ቅስቀሳ በቴፒ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ሦስቱም ቀበሌዎች በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል።

በዕለቱም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች የለውጥ ዓመታቱን የልማትና የመልካም አስተዳደር ስኬቶች የሚያወሱ መልዕክቶችን በማስተጋባት በህብረት ቀበሌ፣በሰላም እና በአንድነት ቀበሌዎች ታላቅ የአደባባይ ቅስቀሳ አካሂደዋል ። ​በሰላም ቀበሌ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ገላቲያስ ሻሜ፤ ፓርቲው ሀገሪቱን መምራት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ አመርቂ ድሎች በሁሉም ዘርፍ ተከናውኗል ብለዋል። በተለይም በቴፒ ከተማ የነበረውን የፀጥታ ችግር በመፍታት የተሟላ ሰላም…

Read More

በ118 ሚለየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የሰንገጢ- ጩርጩራ የመንገድ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ

በዳውሮ ዞን ኢሳራ ወረዳ የተገነባውን የሰንገጢ -ጩርጩራ የመንገድ ፕሮጀክትተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። 40 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው በዳውሮ ዞን ኢሳራ ወረዳ የተገነባውን የሰንገጢ ጩርጩራ መንገድ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) መርቀው ከፍተዋል። መንገዱ የተገነባው ከክልሉ መንግስት በተመደበው 83 ሚለየን ብር እና የዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈፀሚያ በተመደበው 35 ሚለየን…

Read More

የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ አጀንዳዎችን ከመፈጸም ጎን ለጎን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል፦አቶ ፍቅሬ አማን

በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን የክልሉን የዘጠኝ ወራት የፓርቲ የሥራ አፈጻጸም እና 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሥራዎች አስመልክቶ ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል። ኃላፊው በመግለጫቸው፤ በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በፓርቲና መንግሥት የተመሩ የንቅናቄ አጀንዳዎች በተሳካ ሁኔታ መፈጸማቸውን ገልጸዋል። በፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ለአመራሮችና ለአባላት በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎች የአመለካከትና…

Read More