የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት ለግሉ ዘርፍ እኩል ዕድል የሚሰጥ ነው። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ
የመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ስረዓት ለግሉ ዘርፍ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች እኩል የመወዳደር ዕድል በመፈጠር ፍትሀዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርግ እንደሆነ የኢፌዴሪ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ ገልጸዋል። ዋና ዳይሬክተሯ አክለው፥ አዲስ የተዘረጋው የመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት በበየነ መረብ የሚከናወንና በግዥ ስርዓቱ ላይ ግልጽነት የሚፈጠር አሰራር መሆኑን ተናግረዋል። የኤሌክትሮኒክ የግዥ የሚከናወንበት ሲስተም አስተማማኝ የደህንነት ዋስትና ያለው…
