የተረጂነት አስተሳሰቦችን አባላት በመታገል ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ተሳትፏቸው ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ።
ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተሟላ ሉዓላዊነት ለሀገራችን እንደሚያስፈልግ ተገልጿል። ብሔራዊ ክብራችንን ሊያዋርድ በሚችል መንገድ እርዳታዎችን መቀበል እንደማይገባ አቶ የሺዋስ ተናግረዋል ። ኢትዮጵያ የጀመረችውን የለውጥ ጉዞ ለማደናቀፍ ተገዳዳሪ ሀይሎች ጥቃቅን ችግሮችን በመምዘዝ የተለየ የትግል ስልት መፍጠራቸውን አቶ የሺዋስ አስረድተዋል ። አባላት ንቁ ሆነው ማህበረሰቡንም በማንቃት እየተከሰቱ ያሉ ያልተለመዱ ፈተናዎችን ለመሻገር ትኩረት ማድረግ ይገባል ብለዋል። የአስተዳደር ብልጽግና…
