እያደገ የመጣው የኮንፈረንስ ቱሪዝም
እያደገ የመጣው የኮንፈረንስ ቱሪዝም ኢትዮጵያን በአፍሪካ የዲፕሎማሲና የንግድ መድረክ ቀዳሚ ተመራጭ እያደረጋት ይገኛል። መንግሥት ያከናወናቸውን መጠነ-ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችና የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ተከትሎ በዘርፉ መነቃቃት በመፍጠር በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖዎች አሳርፏል። በዚህም የአፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ቱሪዝም መድረክ ተመራጭ መዳረሻ ሆናለች። ለዚህም አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የወዳጅነት…
