ለክልሉ ጂምናስቲክ ልዑካን ቡድን አቀባበል ተደረገለት::
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን በመወከል በኢትዮጵያ ጂምናስቲክ ሻምፒዮና ውድድር ላይ ተሳትፈው ስምንት መዳልያዎችንና አንድ ዋንጫ በማግኘት ውድድሩን ያጠናቀቀው ልዑካን ቡድን ቦንጋ ከተማ ሲደርስ አቀባበል ተደርጎለታል። በአቀባበል መርሐግብሩ ላይ የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ምክት ኃላፊና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አህመዲን አወል፣ የክልሉ ጂምናስቲክ ፌደሬሽን ም/ፕሬዝዳንት አቶ አንተነህ አየለ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።…
