የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ ምላሽ

ሀገራዊ ሪፎርምን በተመለከተ በተለያዩ ዘርፎች ሲከናወኑ የነበሩ ሪፎርሞችን አጠናቀን ሀገራዊ ማንሰራራት የምንጀምርበት ዘመን የመጀመሪያ ምእራፍ ላይ ተገኝተናል፡፡ በመሆኑም በ2017 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ የምናስመዘግብ ይሆናል፡፡ ከዚህ አኳያ ከትናንት እሳቤ ወጥተን በጋራ ወደ ነገ መሻገር አለብን፡፡

Read More

ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የቀረቡ ጥያቄዎች

ከሶማሊላንድ ጋር በተደረገው ስምምነት ተፈጥሮ የነበረውን አላስፈላጊ ውጥረት ለማርገብ የተሰሩ ስራዎችን ቢብራሩ፤ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ማሻሻያ ከመደረጉ በፊት ነባሩ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር በኢኮኖሚያችን ላይ ያስከትላቸው የነበሩ ችግሮች ምን ነበሩ ቢያብራሩልን፣ ማሻሻያው በ2017 በጀት ዓመት የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማሳደግ አንፃር ምን አስተዋፅኦ አለው ተብሎ ይጠበቃል፣ የሃገራችን የፋይናንስ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ዓመታት በሁሉም የአገልግሎት መስኮች ጥሩ ውጤት…

Read More

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል። በስብሰባው ከምክር ቤት አባላት የቀረቡ ጥያቄዎች፤

ሰላማዊ መፍትሄና ህግ የማስከበር ስራ እንዴት ተጣጥሞ ይሄዳል፤ለታጣቂዎችና ለፅንፈኛ ሀይሎች ድጋፍ የሚያደርጉ ፓርቲዎችና አካላትን መንግስት የሚታገሰው እስከ መቼ ነው። በኢንቨስትመንት መሬት አቅርቦት ዙሪያ ያሉ ብልሹ አሰራሮችን ለማስተካከል ምን ታስቦዋል እንዲታረሙስ ምን ታስቦዋል፣ ገዢ ትርክት እንዴት መገንባት ይቻላል፣ ብልሹ አሰራሮችን ለማረምና ለማስተካከል ምን ታስቧል፣ መፈናቀል፣ አግባብነት የሌለው የቤት ፈረሳ አሁን በኮሪደር ልማት ምክንያት የተለያዩ ችግሮች አሉን…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ስብስባ ላይ በምክር ቤቱ አባላት ከተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች መካከል፡-

👉 ከፌዴራል እና ክልሎች በኢንቨስትመንት መሬት አቅርቦት ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች የትኞቹ ናቸው፣ እንዴትስ ሊታረሙ ይችላሉ? 👉 በ2017 በጀት ዓመት የመንግስት ገቢን ለማሳደግ ምን ምን ተግባራትን ለማከናወን ታስቧል? የፋይናንስ ዘርፉ የእስካሁን አፈጻጸም ምን ይመስላል? 👉 በሀገሪቱ የሚስተዋሉ የሰላም እና የጸጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ምን ታስቧል?

Read More

ምክር ቤቱ ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በተገኙበት መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ስብስባውን እያካሄደ ነው፡፡ በስብሰባው ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ። ይህን ተከትሎም ምክር ቤቱ የመንግሥትን አቋም…

Read More

ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎትን ማስፋት የሚያስችል ዘመናዊ የሕክምና መሳሪያ ተደራሽነት ላይ እየተሰራ ነው

ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎትን ማስፋት የሚያስችል ዘመናዊ የሕክምና መሳሪያ ተደራሽነት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ገለጸ። ጤና ሚኒስቴር ለክልሎች፣ ለከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ፣ ለተጠሪ ተቋማትና ለሆስፒታሎች የጤና አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሳልጡ አምቡላንሶችን ጨምሮ 260 ተሽከርካሪዎችን፣ 572 ሞተር ሳይክሎችን፣ 2ሺህ 700 ኮምፒዩተሮችን እንዲሁም የተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ድጋፍ አድርጓል። የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ድጋፉን ለተቋማቱ የሥራ ኃላፊዎች…

Read More

የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ተግባራትን ከገጠር ልማት ኮሪደር ጋር በማስተሳሰር መምራት ይገባል ። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)

የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ተግባራትን ከገጠር ልማት ኮሪደር ጋር በማስተሳሰር መምራት እንደሚገባ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ መዋቅራዊ አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተደርጓል። በምክክር መድረኩ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ የተከናወኑ ተግባራት በተሻለ…

Read More

ኢትዮጵያ የስታትስቲክስ አገልግሎቷን ወደ ዲጂታል ሥርዓት እያሸጋገረች ነው

ኢትዮጵያ የስታትስቲክስ አገልግሎቷን ወደ ዲጂታል ሥርዓት እያሸጋገረች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሯ ይህን ያሉት በ9ኛው የአፍሪካ ስታትስቲክስ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ጠንካራ የስታትስቲክስ ሥርዓት እንዲገነባ እየሰራች መሆኗን አንስተዋል። ለአብነትም በአገር አቀፍ ደረጃ የስታትስቲክስ አገልግሎት ሥርዓቷን ወደ ዲጂታል እያሸጋገረች ነው ብለዋል። የዚህ ዋነኛ ዓላማም የመረጃ ጥራት ለማረጋገጥ፣መረጃ የማግኘት…

Read More

ሀገራዊ የሪፎርም ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ መገናኛ ብዙሃን የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል – ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር)

ሀገራዊ የሪፎርም ስራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ መገናኛ ብዙሃን የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። “ሚዲያ ለብሔራዊ ትርክትና ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለመገናኛ ብዙሃን አመራሮችና ባለሙያዎች ለሶስት ቀናት ሥልጠና ተሰጥቷል። በሥልጠናው የትርክት እመርታ ከታሪካዊ ስብራት ወደ ሀገራዊ ምልዐት፤ እመርታ ከሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ብልጽግና እና የፖለቲካ እመርታ…

Read More