ቻይናን እየጎበኘ ያለው የኢትዮጵያ ልዑክ ከሀገሪቱ ኮሚኒስት ፓርቲ የኦርጋናይዜሽን ዲፓርትመንት ጋር የልምድ ልውውጥ ውይይት አደረገ
በቻይና ጉብኝት እያደረገ የሚገኘውና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የፓርቲው ዋና ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ የተመራው ልዑክ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የኦርጋናይዜሽን ዲፓርትመንት ጋር የልምድ ልውውጥ ውይይት አድርጓል። አቶ አደም ፋራህ በልምድ ልውውጡ፥ ብልጽግና አዲስ ፓርቲ ቢሆንም በመላ ሀገሪቱ መዋቅር ዘርግቶ የተደራጀ ስራ ለመስራትና የአባላቱን አቅም…
