#ኢትዮጵያ_እየመከረች_ነው!

#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚታየውን አመግባባት ለመፍታት አካታች እና አሳታፊ በሆነ መልኩ ምክክር ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያም ይህንኑ አምናበት ሁሉም ዜጎች የሚሳተፉበት ምክክር በማድረግ ላይ ትገኛለች። እርስዎም ሀሳብዎ ለሀገራችን ችግሮች መፍትሄ እንደሚሆን አውቀው በምክክሩ በንቃት ይሳተፉ! ኮሚሽኑ በመጪው እሁድ ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚጀምረው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ የቅስቀሳና…

Read More

ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢን ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ያለው አስተዋጽኦ የላቀ ነዉ። አቶ አልማው ዘውዴ

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢን ማሳደግ ለትምህርት ጥራት ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን ገልጸዋል ። በ2016 ዓ/ም በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር በጨታ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት በበልግ እርሻ 141 ነጥብ 5 ኩንታል የበቆሎ ሰብል ምርት መገኘት መቻሉን…

Read More

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ተቋማት ሚናቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ተመላከተ

ኢትዮጵያ በብሪክስ ማዕቀፍ በንቃት ለመሳተፍ እና በመድረኩ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ ተቋማት የሚኖራቸውን ሚና ማጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ የብሪክስ የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የቴክኒክ ኮሚቴ 5ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዩ የፖሊሲ አማካሪ አምባሳደር ምኒልክ ዓለሙ እንደተናገሩት፤ ጉባዔው የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች አስጠብቋል። ጉባዔው የኢትዮጵያን ጥቅምና ፍላጎቶች ያስጠበቀ፣ አባል ሀገራቱ ለዓለም አቀፍ የፋይናንስ፣ የኢኮኖሚ እና…

Read More

በካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ በጣለዉ ከባድ ዝናብ በተከሰተ የመሬት ናዳ አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸዉ ማለፋን ፖሊስ አስታወቀ

በዞኑ አዲዮ ወረዳግራዋ ሽሽማ ቀበሌ በሌ ልማት ቡድን ተብሎ በሚጠራበት ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት በጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለዉ የመሬት መንሸራተት አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት በመኖሪያ ቤት ዉስጥ እንዳሉ ህይወታቸዉ ማለፋን ፖሊስ ገልጿል። በአደጋዉ ሁለት መኖሪያ ቤቶች በናዳዉ መወሰዱን ያመለከተዉ ፖሊስ በአከባቢዉ የሚጥለዉ ከባድ ዝናብ የነፍስ አድኑን ስራ አስቸጋሪ አድርጎታል።

Read More

የዞኑን ልማት በማፋጠን የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሁሉም ተሳትፎና ርብርብ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

ይህ የተባለው በሸካ ዞን ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ በትኩረት በሚፈፀሙ ተግባራት ላይ ያተኮረ ውይይት በቴፒ ከተማ እየተካሄደ በሚገኝበት ወቅት ነው። የውይይት መድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በወቅቱ እንደተናገሩት የዞኑን ልማትና እድገት ለማፋጠን እንዲሁም የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ርብርብ ወሳኝ ነው ብለዋል። አቶ…

Read More

በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር ይሸፈናል

በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በዘር እንደሚሸፈን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ ወቅታዊ የግብርና መረጃዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም፤ በመኸር እርሻው 20 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች መልማቱን አስታውሰው፤ በሰፋፊ እርሻም ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን…

Read More

በአንደኛው ሩብ ዓመት የተገኘውን ውጤት በማስቀጠል በ2ኛው ሩብ ዓመት የላቀ አፈጻጸም ማስመዝገብ ይገባል። ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር ኢ/ር)።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም እየተገመገመ ነው። የርዕሰ መስተዳድሩ የኢኮኖሚና መሠረተ ልማት ጉዳዮች አማካሪ ዶክተር ኢንጂነር ምትኩ በድሩ የኢኮኖሚ ዘርፍ ተቋማትን የአፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል ። ሪፖርቱን ያቀረቡት አማካሪው በነዚህ ተቋማት ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ተጨባጭ እና ውጤታማ የሆኑ ተግባራት መከናወናቸውን በሪፖርቱ አመላክተዉ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ለይተዉ ለዉይይት አቅርበዋል።…

Read More

አመራሩ ያገኘውን ዕውቀትና ልምድ ወደተግባር በመቀየር ለህብረተሰቡ ለውጥ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።

በኮንታ ዞን “የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ እድገት” በሚል መሪ ሀሳብ ለ10 ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ3ኛ ዙር የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ተጠናቋል። በማጠቃለያው መድረክ ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ሰልጣኞች በነበራቸው ቆይታ በቂ ዕውቀትና ክህሎት ያገኙበት እንደሆነና የ3ኛ ዙር ስልጠና ካለፈው ዓመት ልምድ ተወስዶበት በተሻለ የቀረበበት እንደሆነ አስረድተዋል። የብልጽግና ፓርቲ…

Read More

በኮንታ እና ካፋ ዞኖች በመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸው ላለፉ ዜጎች የክልሉ መንግስት የተሰማውን ልባዊ ሀዘን ይገልጻል ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ትናንት ምሽቱን የጣለው ከባድ ዝናብ በንብረትና በሰው ህይወት ላይ ጉዳት በማድረሱ ማዘኑን ገልጿል። በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ጫሬ ዶቄ ቀበሌ ምሽቱን በጣለው ከባድ ዝናብ የ6 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አስከትሏል። በተመሳሳይ በካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ በደረሰዉ የመሬት ናዳ 4 ሰዎች ህይወት አልፏል። በክልላችን አሁንም ከፍተኛ…

Read More

የህልም ጉልበት፣ ለእመርታዊ እድገት ” በሚል መሪ ቃል በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ላለፉት አስር ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው 3ኛ ዙር የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ በስኬት ተጠናቋል።

በማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ለአመራሩ የሥራ መመሪያ የሰጡት የዳውሮ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታሪኩ አካሉ እንደገለፁት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥና የኅብረተሰቡን ህይወት ለማሻሻል የአመራሩ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው። ህልማችንን ለማሳካት በተገቢው መተለምና የወል ትርክትን በማፅናት እንዲሁም መተግባር ከምንም ጊዜ በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነውም ብለዋል። ከስልጠናው ማግስት ጀምሮ በንድፈ ሃሳብና በመስክ ጉብኝት…

Read More