ርዕሰ መስተዳድሩ ለምክርቤቱ አባላት ባቀረቡት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት በማህበራዊ ልማት ዘርፍ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል ፡፡ከእነዚህም መካከል

የትምህርት ለትውልድ ኢንሼትቭ ስራዎችን ውጤታማ ለማደረግ በጥሬ ገንዘብ፣ በአይነት እና በጉልበት 142,146,033 ብር ተሰብስቧል፡፡ የቱልጊት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉና በክልሉ መንግስት ድጋፍ እየተገነባ ሲሆን ግንባታዉ ከ 90% በላይ ማድረስ ተችሏል፡፡ የትምህርት ተሳትፎ ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል 734,496 ተማሪዎች በመማር ላይ መሆናቸው፡፡ የአንደኛ ደረጃ መማሪያ መጽሐፍ በህብረተሰብ ተሳትፎ ብር 161,205,719 እና…

Read More

ርዕሰ መስተዳድሩ ለምክርቤቱ አባላት ባቀረቡት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት በመሠረተ ልማት ዘርፍ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል ፡፡

የአርብቶና ከፊል አርብቶ አደር ልጆችን በሆስቴሎች 179 ተማሪዎች ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ መሆናቸው በአርብቶ አደር አካባቢ የሚታየውን የተማረ የሰው ኃይል እጥረት ለመቅረፍ በመጀመሪያ ዲግሪ 116 እና በዲፕሎማ 42 ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ መሆኑ በአነስተኛ የመጠጥ ውሃ ስራዎች የምንጭ ግንባታ ቤሮ ወረዳ ሲሪት ቀበሌ፣ ሜ/ሻሻ ወረዳ ቂራ ቀበሌ፣ ሜ/ሻሻ ወረዳ ጎሪነሱ ቀበሌ፣ ሜ/ሻሻ ወረዳ ቦኡት ቀበሌ 100% የተጠናቀቁ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 7ኛመደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነዉ ፡፡

በጉባኤው የክልሉ መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የአፈጻጻም ሪፖርት በርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በመቅረብ ላይ ይገኛል ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ለምክርቤቱ አባላት ባቀረቡት የ6 ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት በኢኮኖሚው ልማት ዘርፍ የተሻሉ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል ፡፡ ርዕሠ መስተዳድሩ ካነሱዋቸው ነጥቦች መካከል፡- በመኸር የግብርና ሥራዎች አዝመራ በተከናወነ ተግባር 384 ሺህ 786 ሄክታር የማሣ ሽፋን ተከናውኗል…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ በጉባዔዉ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር ምክርቤቱ ባለፉት 6 ወራት በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ኃላፊነት ለመወጣት የተለያዩ ጥረቶች ማድረጉን ተናግረዋል ፡፡ የክልሉ ምክር ቤት ከፍተኛ የህግ አውጭ አካል በመሆኑ የፌዴራሉን ህገ መንግስት በማይጻጸር መልኩ በክልሉ ውስጥ ተፈጻሚ የሚሆኑ ህጎችን የማውጣት፣የአስፈጻሚ አካላትን ተግባር የመከታተልና የመቆጣጠር ስራዎችን ሲከናውን መቆየቱን አፈ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነዉ ፡፡

በጉባኤው የተለያዩ አጀንዳዎች ቀርበው እንደጸድቁም ከወጣው የድርጊት መርሃ ግብር ማወቅ ተችሏል ፡፡ ከታርጫ ከተማ የሚካሄደው ይኸው ጉባኤ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በቀጥታ ከስፍራው እየተሰራጨ ነዉ፡፡ በታጠቅ አበበ

Read More

የክልሉ መንግሥት የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ከመገምገም ባሻገር ቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በመወያየት አቅጣጫ አስቀምጧል።የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳች ቢሮ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የክልሉ መንግሥት የ2017 በጀት ዓመት 1ኛው ግማሽ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ አድርጎ ያስቀመጣቸው ጉዳዮችን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል። የክልሉ መንግሥት የ2017 በጀት ዓመት 1ኛው ግማሽ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን…

Read More

በህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ላይ የህግ በላይነት ለማረጋገጥ ይሰራል፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት “ህገወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመከላከል በጋራ እንተጋለን!” በሚል መሪ ቃል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ ውይይት አካሂዷል። በዉይይት መድረኩ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ መበራከት በክልሉ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና የፖለቲካ ያለመረጋጋት እንዲፈጠር አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ በህገወጥነት የተሳተፉትን ተጠያቂ ማድረግ እና የህግ በላይነት ማስከበር…

Read More

የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ለማስተናገድ ዝግጅት ተደርጓል- ብሔራዊ የዝግጅት ኮሚቴ

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ለማስተናገድ የተሟላ ዝግጅት መደረጉን የብሔራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ። ጉባኤውን በስኬት ለማከናወን 35 ተቋማትን ይዞ የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ የቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቂያ በተመለከተ በጋራ ማብራሪያ ሰጥቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታና የኮሚቴው ሰብሳቢ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እንዳሉት፣ ለ38ኛው የአፍሪካ ህብረት…

Read More

አካታችነት በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት

አካታችነት በፅንሰ-ሀሳብ ደረጃ ሲታይ በብዙ ዓውድ ውስጥ ሊገቡ የሚችሉ ትንታኔዎችን ይይዛል፡፡ እንደ መነሻ ይሆነን ዘንድ ፅንሰ-ሀሳቡን ሊያብራሩልን የሚችሉ ትንታኔዎችን ስንመለከት አብዛኛዎቹ የሚጋሩት ሀሳብ አካታችነት በተለያዩ ደረጃዎች ሊገለጹ የሚችሉ ልዩነቶችን እና ብዘሀነትን እንደሚያስተናግድ የሚተነትኑ መሆናቸው ነው፡፡ ሆኖም ግን አካታችነት በዕድሜ፣ በጾታ፣ በዘር፣ በሀይማኖት፣ በኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ወዘተ የተለዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በአንድ ሂደት ውስጥ እንዲሳተፉ ከማድረግም የዘለለ ፅንሰ-ሀሳብን…

Read More

በሰብል ምርታማነት የተመዘገበው ስኬት ለአግሮ-ኢንዱስትሪ ሽግግር ምቹ መደላድል ፈጥሯል – ግብርና ሚኒስቴር

በሰብል ምርታማነት የተመዘገበው ስኬት ከውጭ የሚገቡ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በመተካት ለአግሮ-ኢንዱስትሪ ሽግግር ምቹ መደላድል መፍጠሩን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ። በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ኢሳያስ ለማ፤ በ2016/17 ዓ.ም የምርት ዘመን በሰብል ከተሸፈነው ከ20 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት 608 ሚሊየን ኩንታል ምርት ይጠበቃል ብለዋል። በእስካሁኑ ሂደትም በምርት ዘመኑ የመኸር እርሻ ሰብል 505 ሚሊየን ኩንታል ምርት…

Read More