ከ740 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በቦንጋ ከተማ የተገነባው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ተመረቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ቀጠና ግብርናን ለማዘመን ታስቦ በቦንጋ የተገነባው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል እ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመኒቴ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቀው ተከፍቷል። ኮርፖሬሽኑ በቦንጋ ከተማ በ743 ሚሊዮን ብር፣ በ2.5 ሄክታር መሬት ላይ ያስገነባው ማዕከሉ በውስጡ ባለ አራት ወለል የአስተዳደር…

Read More

የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት የሚቀርፍ ነው። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለግብርና ስራው መሠረታዊ ችግር የኾነውን የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግር በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ግብርናውን ለማዘመን በሰጡት ልዩ ትኩረት ተገንብተው ለአግልግሎት የበቃው ማዕከሉ በአጠቃላይ በክልሉ የግብርና ግብዓት በማሳለጥ እና የግብርና…

Read More

ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲ የትኩረት አቅጣጫ ነው – ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)

ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን እውን በማድረግ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ። በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባዔ ባለፉት ሦስት ዓመታት ፓርቲው ለሕዝብ የገባውን ቃል በብዙ ጥረትና የተቀናጀ ሥራ እያሳካ እንደቆየ ተገምግሟል። ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)÷ብልጽግና ከዚህ በፊት የጀመረውን ዘርፈ ብዙ የልማትና የእድገት ሥራዎች…

Read More

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ አዲስ አበባ ገቡ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሺዴ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ እና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ በኢትዮጵያ ቆይታቸው፥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከከፍተኛ የመንግስት…

Read More

በተቀናጀና በተሟላ የግብርና ፓኬጅ ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራሁ ነው፦ ኮርፖሬሽኑ

ግብርናውን በተቀናጀና በተሟላ ፓኬጅ ተግባራዊ በማድረግ ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ገለፃ። የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወ/ማርያም በቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ተገኝተው ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአስር ዓመቱ መሪ የግብርና እቅድ መነሻ የግብርና ግብዓት አግልግሎት አቅርቦት ተደራሽነት ለማስፋፋት በመላው…

Read More

በብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ገቢራዊ በማድረግ የክልሉን ህዝብ ዘላቂ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል።አቶ ማስረሻ በላቸው

የብልጽግና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ሁለተኛውን የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ተከትሎ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ተፈጻሚ ከማድረግና የህዝቡን የልማት ፍላጎት ከግብ ለማድረስ የተያዘውን ቁርጠኝነት አስመልክቶ ከሚዲያዎች ጋር ቆይታ አድርጓል። በቆይታቸዉ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚተገበሩም አብራርተዋል ። በብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ የተቀመጡ…

Read More

ክልሉ ያለው አቅም የሀብት ምንጭ እንዲሆን መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የስራ ኃላፊዎች ገለጹ

በሚቀጥሉት 3 ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ሊተገበሩ በታቀዱ ሥራዎች ዙሪያ በቦንጋ አተማ ውይይት ተደርጓል። ውይይቱ “ከዕምቅ አቅም ወደሚጨበጥ ሀብት” በሚል መሪ ቃል በክልሉ መንግስት የተዘጋጀ የፖለቲካና የልማት ውይይት ሲሆን ፤ ክልሉ ለቀጣይ ትውልድ የሚተላለፉ በርካታ ሀብቶች ባለቤት መሆኑ ተገልጿል። በክልሉ ያሉ የመልማት አቅሞችን በተገቢው መለየትና መጠቀም፣ ህብረተሰቡን በማስተባበር ልማታዊ ስራዎችን ማጠናከር፣ የአመራሩን እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን…

Read More

በክልሉ ለጤና ልማት ሥራዎች ትኩረት በመስጠት የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን በማረም የማህበረሰቡን ጤና ማስጠበቅ ይገባናል ሲሉ ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት የሚዛን አማን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የ2017 በጀት ዓመት ክልላዊ ማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት” የጤና መድህን አገልግሎት ለጋራ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሂደዋል። በመድረኩ የ2017 በጀት ዓመት የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት የእስካሁን አፈጻጸምና ማቀጣጠያ ንቅናቄ ሰነድ ቀርበው ውይይት…

Read More

የውስጠ ፓርቲ አንድነትና ጤንነት በማስጠበቅ ረገድ አመራርና አባሉ ምሳሌ መሆን አለበት። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ የስድስት ወራት አፈጻጸም በቦንጋ ከተማ ተገምግሟል። በፖለቲካና በአደረጃጀት ዘርፎች እንዲሁም በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ከእቅዱ መነሻ በርካታ ተግባራት መፈጸማቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል። በግምገማው መድረክ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የውስጠ ፓርቲ አንድነትና ጤንነት በማስጠበቅ ረገድ አመራርና አባሉ ምሳሌ መሆን መቻል እንዳለበት…

Read More

12 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ በኦሚያ ቀበሌ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ 3162 ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል ።

በምረቃው ስነስርዓት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው እንደገለጹት የኦሚያ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ በ2011 ዓ/ም ተገንብቶ ለዓመታት ሳይጠናቀቅ በመቆየቱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ መቆየቱንና አሁን ላይ ግንባታው ተጠናቅቆ ለአገልግሎት መብቃቱ የህዝቡን ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል። በክልሉ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ ተጀምረው የተቋረጡ የንጹህ መጠጥ ውሃ…

Read More