Trendings

3.4 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፦ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

በዘጠኝ ወራት ውስጥ 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ገልጸዋል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የዳመጠ ሲሆን፤ የምክር ቤት አባላት በርካታ ጥያቄዎች አቅርበው ሚኒስትሯ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በዚሁ…

Read More

ሁሉን አካታች የሰላም ግንባታ እንዲኖር በትኩረት ይሰራል – ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

ሴቶች፣ ወጣቶችና ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች በሀገር ሰላም ግንባታ ያላቸውን ሚና የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) ገለጹ። “ሰላምን ተለማመዱ በሰላም ኑሩ” የተሰኘ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል። ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር) በዚህ ወቅ እንዳሉት÷ሴቶች፣ ወጣቶችና ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች በሰላም ግንባታ ሒደት ላይ እንዲሳተፉ እየተሰራ ነው። ሰላምን በመገንባት ሥራ የአመራር ሚና እንዲኖራቸው ትኩረት መደረጉን ጠቁመው÷ማህበራዊ ትስስርን ማጠናከር…

Read More

ሜክሲኮ ከኢትዮጵያ ጋር በግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር በትብብር እንደምትሰራ ገለጸች

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የሜክሲኮ አምባሳደር አሊሃንድሮ ኢስቲቪል ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት፥ ኢትዮጵያ ከአምስት ዓመታት በፊት የዝናብ ጥገኛ የነበረውን የስንዴ ልማት በአሁኑ ወቅት በመስኖ በስፋት እያመረተች መሆኑን አንስተዋል፡፡ የአርሶ አደሩን የሜካናይዜሽን ፍላጎት ለማሟላት የሜክሲኮ ባለሃብቶች ተሰማርተው ምርቶችን በማቀነባበርና ግብርናውን በማዘመን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። ሜክሲኮ በበቆሎና ስንዴ ማሻሻያ ማዕከል የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ…

Read More

በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የጸደቀዉ የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362/ 2017 የጤና ባለሙያዎችን የረጅም ግዜ ጥያቄ የሚመልስ ነዉ።

በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የጸደቀዉ የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362/ 2017 ከጤና አገልግሎትና አስተዳደር ጋር ተያይዞ ከሀረብረተሰቡና ከጤና ባለሙያዎች የሚነሱ ተገቢ የሆኑ ብዙ ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ ትልቅ መሰረት የጣለና ብዙ ማነቆዎችን ለመፍታት የሚያስችል ነዉ። ከነዚህም ዉስጥ ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮችን ብቻ እንኳን ብናይ:- 1/ የጤና ዘርፍ ሰራተኛ መብት በሚደነግገዉ አንቀጽ ስር የጤና…

Read More

ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው የኢኮኖሚ ዕድገት ለሌሎች አርአያ መሆን እንደሚችል ፓኪስታን ገለጸች

በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ከፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር የውጭ ግንኙነት ልዩ አማካሪ ሰይድ ታሪቅ ፋጢሚ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሀገራቱ ሰላም፣ ብልጽግና እና የዘላቂ ልማት የጋራ ግቦችን ለማሳካት የባለብዙ ወገን ትብብርን ጨምሮ በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ሁለቱ ወገኖች በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ አቪዬሽን፣ ቴክኖሎጂና አየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። አምባሳደር…

Read More

የውስጥ ጥንካሬ እና አቅም ለውጭ ግንኙነት ስኬታማነት ፋይዳዉ የላቀ ነው፦የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

የውስጥ ጥንካሬ እና ዐቅም ለውጭ ግንኙነት ስኬታማነት ፋይዳዉ የላቀ በመሆኑ በዚህ ላይ አተኩሮ መሥራት እንደሚገባ የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡ “ዓላማ ተኮር ተግባቦት ለኢትዮጵያ መንሰራራት” በሚል መሪ መልዕክት ለኮሙኒኬሽን ዘርፉ የክልል እና ከተማ አስተዳደር መዋቅር አመራሮች እና ከፍተኛ ባለሙያዎች በአዲስአበባ እየተሰጠ ያለው ሥልጠና በሁለተኛ ቀን ውሎዉ ጂኦ-ፖለቲካዊ ዓውዶች እና የውጭ…

Read More

ሪፖርታዥ

የክልላችን የበልግ ስራ እንቅስቃሴ በሀገራችን ታርክ የግብርናው ዘርፍ በኢኮኖሚው ለረጅም ዓመታት ብቻውን የመሪነት ሚና ሲጫወት መቆየቱና አሁንም ትኩረት ከተሰጣቸው የብዝሀ ኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብዙ ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት ነው። ከነዚህም አንዱና ጉልህ ሚና ያለው የክልሉ ግብርና እና የተፈጥሮ ዘርፍ ነው። የክልል ግብርና ቢሮው የተፈጥሮ ሀብት እንዳይጎዳ በመጠበቅ፣…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ኮንፈረንስ እና ግምገማ መድረክ ጎን ለጎን የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኙ

በጉብኝቱ የቦንጋ የግብርና ምርምር ማዕከል የተለያዩ የምርምር ውጤቶች የሆኑትን የሙዝ፣የዶሮ እርባታ፣የንብ ማነብ፣ችግኝ ጣቢያ፣ የእንሰሳት መኖ፣ የስራስር ምርቶች ፣እንዲሁም ሌሎች የምርምር ውጤቶችን ምልከታ ተካሂዷል። የምርምር ማዕከላት በዘር ብዜት እና በቴክኖሎጂ በማፍለቅ ፣በተፈጥሮ ሀብት እና በእንስሳት እርባታ ማላመድና በማስተዋወቅ ረገድ ለአርሶና አርብቶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በርካታ ስራዎች እየተሰራ መሆኑን በጉብኝቱ ገለጻ ተደርጓል። በጉብኝቱ የክልሉ…

Read More

ከብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ

ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ሚያዝያ 1 ቀን 2017 ባደረገው ስብሰባ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለማዊ ሁኔታዎችን ገምግሟል፡፡ ኢትዮጵያ ለዘመናት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ስብራቶች ገጥመዋት ነበር፡፡ እነዚህን ስብራቶች በመጠገን ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ እያፋጠነች ትገኛለች፡፡ እስካሁን የጀመረቻቸው ሪፎርሞች እየተሳኩ፤ የወጠነቻቸው ኢኒሼቲቮች ፍሬ እያፈሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላት ተሰሚነት እየጨመረ፤ ብሔራዊ ጥቅሞቿን ለማስከበር የምታደርገው ጥረት ውጤት እያስመዘገበ…

Read More

የደቡብ ሞዕራብ ኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ያዘጋጀው የምርምር ስራዎች ኢግዚቢሽን ተከፈተ

በተቋሙ እስካሁን 218 ቴክኖሎጂዎችና እና መረጃዎችን በሰብል፣ በተፈጥሮ ሀብት እና በእንስሳት እርባታ ማላመድና ማፍለቅ መቻሉ የተገለጸ ሲሆን ከነዚህ ዉስጥ 123 ቴክኖሎጂዎችን በማሸጋገር ለተጠቃሚ አርሶና አርብቶ አደሮች ማድረስ መቻሉን ተነግሯል። ኢንስቲትዩት በቦንጋ ከተማ ባዘጋጀው አመታዊ የምርምር ስራዎች ኮንፈረንስ ላይ በሰብል፣ በተፈጥሮ ሀብት እና በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰሩ የምርምር ውጤት ኢግዚቢሽን ለዕይታ አብቅቷል። የኮንፈረንሱ ታዳሚዎች በኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎች…

Read More