የናይጄሪያ ወታደራዊ ልዑክ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የለውጥ ሥራዎችን ጎበኘ
የናይጄሪያ ወታደራዊ ሪሶርስ ማዕከል ልዑካን ቡድን አባላት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም፤ ዘመናዊ የፖሊስ መገናኛ ዲጂታል ሬድዮ፣ የኮማንድ ኮንትሮል ማዕከልን፣ የቀጥታ ጥቆማ መቀበያ፣ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያና ዘመናዊ ካሜራና የደኅንነት መሣሪያ የተገጠመላቸው ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎችን ተመልክተዋል፡፡ የተቋሙን ተልዕኮ፣ አደረጃጀት፣ እሴቶችና ዓላማ በተመለከተ የፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ዋና መምሪያ ተጠባባቂ…
