ከ61ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ህብረተሰቡ ተቀላቅለዋል – ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን
ባለፉት ጊዜያት ከ61ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ህብረተሰቡ መቀላቀላቸውን ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ገለጸ። ኮሚሽኑ ከስዊድን መንግስት ጋር በመተባበር ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአማራ፣ ከአፋር እና ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ለተውጣጡ የባለድርሻ አካላት የአሠልጣኞች ስልጠና በአዲስ አበባ መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው ታጣቂዎችን በመልሶ ማቋቋም፣ በኢንተርፕርነርሺፕና በስራ ፈጠራ ዙሪያ የሚያተኩር ሲሆን ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይም ተጠቁሟል። በዚሁ ወቅት…
