የክልሉን ሕዝቦች የጤና ደህንነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ማስመዝገባቸውን ቢሮው አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከተጠሪ ተቋማቱ ጋር በመሆን በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የእናቶችና ሕፃናት ጤና አገልግሎት፣ የወባ በሽታ ጫና መቀነስና የጤና መድህን ተደራሽነትን በማረጋገጥ ረገድ ስኬታማ ተግባራት ማከናወኑን አስታወቀ። የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደገለጹት፤ በክልሉ የእናቶችንና የሕፃናትን ጤና ለመጠበቅ በተደረገው ጥረት የቅድመ ወሊድ ክትትል አገልግሎት ከፍተኛ ውጤት…
