ሚዲያዎች የእውነት ምንጭ እና የሀገር መንፈስ መሆን አለባቸው – ብልፅግና ፓርቲ

ሚዲያዎች ሙቀት ሳይሆን ብርሃን መፍጠር ላይ ማተኮር፤ ጫጫታ ላይ ሳይሆን የእውነት ምንጭ እና የሀገር መንፈስ መሆን አለባቸው አለ ብልፅግና ፓርቲ። ፓርቲው “ሚዲያ የሀገር መንፈስ ነው” በሚል መሪ ሐሳብ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል። ዓለም አቀፍ የሚዲያ ቀንን ምክንያት በማድረግ “የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በተከታታይ ሳምንታት ሲካሄዱ የቆዩ ሚዲያ ላይ ያተኮሩ መድረኮች…

Read More

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤት ከቀረቡ ዕጩዎች ጋር ምክክር እየተካሄደ ነው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤት በብልፅግና ፓርቲ የቀረቡ ዕጩ ተወዳዳሪዎች ጋር በቀጣይ ተልዕኮዎች ዙሪያ በቦንጋ ከተማ ምክክር እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ የክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማንና ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውን ጨምሮ ሌሎች…

Read More

በሸካ ዞን ግብርናን ለማዘመን የሚያስችሉ የ117 ሚሊዮን ብር የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉና ከ117 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቁ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል። በክልሉ የግብርና ቢሮ በምግብ ስርዓተ ማጠናከሪያ ፕሮግራም ድጋፍ የሚገነቡትን የእነዚህን ፕሮጀክቶች መሠረተ ድንጋይ ያስቀመጡት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ናቸው። በዞኑ ያለውን እምቅ የግብርና አቅም ወደ ተሻለ ደረጃ…

Read More

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ፣ ሁሉም ፓርቲዎች ለምርጫው ስኬት በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ተጠየቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የተፎካካሪ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውይይት በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በጋራ ምክር ቤቱ የውይይት መድረክ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፤ በክልሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ግንባታ ላይ በትብብር መስራት ይገባል ብለዋል። መጪው ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግርና የሀገረ መንግስት ግንባታው…

Read More

በዳውሮ ዞን የሎማ ቦሳ ወረዳና የገሳ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ በሰልፍ እየገለጹ ነው

​በዳውሮ ዞን የሎማ ቦሳ ወረዳ እና የገሳ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች የብልጽግና ፓርቲን ዓላማና እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን በመደገፍ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ ማካሄድ ጀምረዋል። ​ዛሬ ረፋዱን በገሳ ከተማ በተጀመረው በዚህ ሰልፍ ላይ የየአካባቢው ነዋሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች በነቂስ ወጥተው ድጋፋቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ሰልፈኞቹ የፓርቲውን ዓላማ የሚደግፉና የመንግሥትን የለውጥ ጉዞ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ መፈክሮችን እያስተጋቡ ነው።…

Read More

ምርጫ የህዝብ ፍላጎት የሚገለጽበት ከፍተኛ ሀገራዊ ሂደት በመሆኑ ሁሉም አካላት በህግ መሠረት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የክልሉ የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን አስታወቀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የስነ-ምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን በምርጫ ስነምግባር እና በሀብት ምዝገባ ዙሪያ ለስር መዋቅሮች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ እንደገለጹት፤ የስልጠናው ዋና ዓላማ የምርጫ ሥነ_ምግባር መመሪያን በጥልቀት በመረዳት ለመተግበር የሚያስችል አቅም ለመገንባት ያለመ ነው። 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በክልላችንና በፌዴራል ደረጃ የሚካሄድ ትልቅ ሀገራዊ ሂዳት ነው ያሉት ኮሚሽነር…

Read More

የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶቹ የህዝብን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የተፎካካሪ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት አባላት በቦንጋ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኮርደር ልማት እና የመሰቦ አንድ ማዕከልን ጎብኝተዋል። የልማት ፕሮጀክቶችን በስፍራው ተገኝተው የተመለከቱ የጋራ ምክር ቤቱ አባላት ፤ እየተከናወኑ ያሉ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል። እንደ አባላቱ ገለጻ፣ መሰል የልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው የዴሞክራሲ ስርዓቱን በጽኑ…

Read More

ጉባኤው በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ የጋራ ድምጽ ማሰማት የሚቻልበትን ዕድል ማመቻቸት ነው

የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባዔ (ASMIS) ዋነኛ ዓላማም በተፅዕኖ ፈጣሪዎች መካከል ጠንካራ ትብብር በመፍጠር በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ የጋራ ድምጽ ማሰማት የሚችሉበትን ዕድል ማመቻቸት እንደሆነ የፐልስ ኦፍ አፍሪካ አስተባባሪ አቶ በረከት ሲሳይ ገለጹ። የአፍሪካውያንን አጀንዳ ለማስረፅና የጋራ ድምፅን ለማሰማት ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም አክለዋል። ፐልስ ኦፍ አፍሪካ (Pulse of Africa-POA) ከ ኤ.ጂ.ኤ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዝ (AGA-Tech) ጋር…

Read More

የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለጠንካራ ሀገር ግንባታ እያደረጉ ያለውን አስተዎጽኦ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በቤንች ሸኮ ዞን እየተሰሩ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት በገበታ ትውልድ መርሃ ግብር የተመረቀው የደንቢ ኢኮ ሎጅን፣ የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ፣የደቡብ ምዕራብ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴውን ተዘዋውረው ተመልክዋል። የምክር ቤቱ አባላት በየአከባቢው እየተከናወኑ…

Read More

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የአገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ማዕከል ባደረገ መልኩ እየተገነባ ነው

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የአገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ማዕከል ባደረገ መልኩ እየተገነባ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየውን የ”ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ በይፋ መክፈታቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ በዘንድሮው “ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ ላይ የሀገራዊ ርዕያችንን ተጨባጭ ስኬት መመልከት…

Read More