የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ነው
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ተገቢና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በኢትዮጵያ የኖርዌይ እና የባንግላዲሽ አምባሳደሮች ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቅርቡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ኢትዮጵያና ቀይ ባሕር በሕግ፣ በመልክዓምድር፣ በታሪክና ሌሎች መለኪያዎች ሊነጣጠሉ እንደማይችሉ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስቴንሰን እና በኢትዮጵያ የባንግላዲሽ አምባሳደር ኤር ቫይስ ማርሻል ሲትዋት ናይም ለኢዜአ…
