ታሪካዊ የባሕር በር መብታችንን ለማረጋገጥ የበኩላችንን እንወጣለን፡- ብሔራዊ የኢትዮጵያ ሠራዊት ማኅበር
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ሠራዊት ማኅበር ወቅታዊ በሆነው የሀገሪቱ የባሕር በር አጀንዳ ላይ የፓናል ውይይት አካሄደ። በውይይቱ ላይ የማኅበሩ አባላት፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ብርሃኑ አማረ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፤ የባሕር በር ጉዳይ ሀገራዊ አጀንዳ እንዲሆን በማድረጋቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምስጋና አቅርበዋል። “ኢትዮጵያና ቀይ ባሕር ተነጣጥለው አያውቁም” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ በታሪክ አጋጣሚ…
