በክልሉ ዘላቂ የጤና፣ ምግብና የትምህርት ልማት ሥራዎችን ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የተባበሩት መንግስታት የዓለም ዓቀፍ የልማት አጋር ድርጅቶች ገለጹ
የተለያዩ የተባበሩት መንግስታት የዓለም ዓቀፍ የልማት አጋር ድርጅቶች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የቀጣይ ድጋፍ አቅጣጫ ለመለየት ያለመ የልማት ሥራዎች ጉብኝት እና ከክልሉ መንግስት ጋር ውይይት ማድረጋቸው የሚታወስ ነዉ። የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) የኢትዮጵያ ተወካይ ዶ/ር ፍራንሲስ ቺሳካ፤ በክልሉ በነበራቸው ቆይታ በክልሉ ያለውን እምቅ አቅም መመልከታቸውን ገልጸዉ በተለይም በትምህርት ቤቶች የተመለከቱት የተማሪዎች ምገባ መርሐግብር…
