BLOGS
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ኮንፈረንስ እና ግምገማ መድረክ ጎን ለጎን የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኙ
በጉብኝቱ የቦንጋ የግብርና ምርምር ማዕከል የተለያዩ የምርምር ውጤቶች የሆኑትን የሙዝ፣የዶሮ እርባታ፣የንብ ማነብ፣ችግኝ ጣቢያ፣ የእንሰሳት መኖ፣ የስራስር ምርቶች ፣እንዲሁም ሌሎች የምርምር ውጤቶችን ምልከታ ተካሂዷል። የምርምር ማዕከላት በዘር ብዜት እና በቴክኖሎጂ በማፍለቅ ፣በተፈጥሮ ሀብት እና በእንስሳት እርባታ ማላመድና በማስተዋወቅ ረገድ ለአርሶና አርብቶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ በርካታ ስራዎች እየተሰራ መሆኑን በጉብኝቱ ገለጻ ተደርጓል። በጉብኝቱ የክልሉ…
ከብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ
ብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ሚያዝያ 1 ቀን 2017 ባደረገው ስብሰባ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለማዊ ሁኔታዎችን ገምግሟል፡፡ ኢትዮጵያ ለዘመናት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ስብራቶች ገጥመዋት ነበር፡፡ እነዚህን ስብራቶች በመጠገን ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ እያፋጠነች ትገኛለች፡፡ እስካሁን የጀመረቻቸው ሪፎርሞች እየተሳኩ፤ የወጠነቻቸው ኢኒሼቲቮች ፍሬ እያፈሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላት ተሰሚነት እየጨመረ፤ ብሔራዊ ጥቅሞቿን ለማስከበር የምታደርገው ጥረት ውጤት እያስመዘገበ…
የደቡብ ሞዕራብ ኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ያዘጋጀው የምርምር ስራዎች ኢግዚቢሽን ተከፈተ
በተቋሙ እስካሁን 218 ቴክኖሎጂዎችና እና መረጃዎችን በሰብል፣ በተፈጥሮ ሀብት እና በእንስሳት እርባታ ማላመድና ማፍለቅ መቻሉ የተገለጸ ሲሆን ከነዚህ ዉስጥ 123 ቴክኖሎጂዎችን በማሸጋገር ለተጠቃሚ አርሶና አርብቶ አደሮች ማድረስ መቻሉን ተነግሯል። ኢንስቲትዩት በቦንጋ ከተማ ባዘጋጀው አመታዊ የምርምር ስራዎች ኮንፈረንስ ላይ በሰብል፣ በተፈጥሮ ሀብት እና በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰሩ የምርምር ውጤት ኢግዚቢሽን ለዕይታ አብቅቷል። የኮንፈረንሱ ታዳሚዎች በኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎች…
የናይጄሪያ ወታደራዊ ልዑክ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የለውጥ ሥራዎችን ጎበኘ
የናይጄሪያ ወታደራዊ ሪሶርስ ማዕከል ልዑካን ቡድን አባላት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት የለውጥ ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም፤ ዘመናዊ የፖሊስ መገናኛ ዲጂታል ሬድዮ፣ የኮማንድ ኮንትሮል ማዕከልን፣ የቀጥታ ጥቆማ መቀበያ፣ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያና ዘመናዊ ካሜራና የደኅንነት መሣሪያ የተገጠመላቸው ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎችን ተመልክተዋል፡፡ የተቋሙን ተልዕኮ፣ አደረጃጀት፣ እሴቶችና ዓላማ በተመለከተ የፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ትብብር ዋና መምሪያ ተጠባባቂ…
ኢንስቲትዩቱ 123 ቴክኖሎጂዎችን በማሸጋገር ለተጠቃሚ አርሶና አርብቶ አደሮች ማድረስ ተችሏል።
የደቡብ ሞዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርሞር ኮንፈረንስ ግምገማ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት ከተሰጣቸው የኢኮኖሚ መሠረቶች አንዱ የግብርና ክፍሌ ኢኮኖሚ መሆኑን የገለጹት የክልሉ የመንግሥት ረዳት ተጠሪ አቶ ነጋ አበራ ኢንስቲትዩቱ ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ ያለው አበረታች ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የክልሉን የግብርና እምቅ አቅም በተገቢው…
በሲስተም መቋረጥ ምክንያት በተፈጠረው የክፍያ መዘግየት የሚቋረጥ አገልግሎት አይኖርም – የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ሰሞኑን በተፈጠረው የሲስተም ችግር መነሻነት በሚፈጠር የአገልግሎት ከፍያ መዘግየት ምክንያት ተጠቃሚዎች አገልግሎት እንደማይቋረጥባቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። ካለፉት ሦስት ቀናት ጀምሮ ሲስተም ላይ ባጋጠመ ቴክኒካል ችግር ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎች እንዲሁም የዲጂታል ክፍያ አማራጮች ላይ የአገልግሎት መቋረጥ ማጋጠሙን አገልግሎቱ አስታውሷል። የተቋረጠውን አገልግሎት በአጭር ጊዜ ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን እና ደንበኞች ያጋጠመውን…
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ አራት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዶላር ተመዝግቧል
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የዘጠኝ ወርጨ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እየገመገመ ይገኛል። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የንግድ ከባቢዉን ምቹ ለማድረግ እሰፋፊ ስራዎች ተከናዉነዋል። በዚህም በኢትዮጵያ በዉጪ ንግድ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ አራት ነጥብ አምስት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኑሮ ዉድነቱን ለማረጋጋት በሰራዉ ስራም በዘጠኝ ወሩ…
የደቡብ ሞዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ኮንፈረንስ ግምገማ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በምርምር ኮንፈረንሱ የክልሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ግብር ምርምር ኢንስቲትዩት ተወካዮች፣ የምርምር ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ የተለያዩ ተመራማሪዎች፣ በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተወካዮች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል። በምርምር ኮንፈረንሱ ላይ በተለያዩ ተመራማሪዎች የተሰሩ የምርምር ስራዎች ግምገማ እንዲሁም የምርምር ስራዎች ኢግዚቢሽን እንደሚካሄድ ከወጣሁ መርሀግብር መመልከት ተችሏል። በዕድገቱ በዛብህ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ሊያከብር ነው
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን የእስካሁን ታሪኩንና የወደፊት ተልዕኮውን በሚመጥን መልኩ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) አስታወቁ። ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ የዩኒቨርሲቲውን የራስ ገዝነት የሪፎርም አፈጻጸም እና የ75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ አከበባርን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወጣው የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረት…
