በክልሉ የተጎዱ መሬቶችን የማገገምና የአካባቢ ጥበቃ ስራ በልዩ ትኩረት እየተከናወነ መኾኑ ተገለፀ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሸካ ዞን የኪ ወረዳ በአርሶ አደር መር የተፈጥሮ ሀብት ማገገሚያ ፕሮጀክት አማካኝነት የተጎዱ መሬቶችን የመንከባከብ እና የችግኝ ተከላ ተካሂዷል። የክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና የአነስተኛ መስኖ ዳይሬክተር አቶ አሚኖ መሐመድ እንደገለጹት፤ የዚህ ንቅናቄ ዋና ዓላማ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ በደን በመሸፈን የአፈር ለምነትን ማሳደግና የአርሶ አደሩን ምርታማነት ማረጋገጥ ነው። ፕሮጀክቱ…
