የፐብሊክ ሰርቪስ አገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም የሰራተኞችን ጥቅም ከማስከበር ባሻገር የተገልጋዩን እርካታ በማሳደግ ምርታማነትን የማሳደግ ዓላማን ያነገበ መሆኑ ተገለፀ።
የጤና ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም አተገባበር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። በስልጠና መድረኩ ላይ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊስ ላይ ስልጠና የሰጡት የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ የሲቪል ሰርቪሱ ሪፎርም ነፃ፣ ገልለተኛና ብዝሃነት ላይ ያተኮረ ተቋማት በመገንባት የሀገረ መንግስት ግንባታን ማጽናት መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም ትክክለኛውን…
