Trendings

“በሁሉም አካባቢ የሚኖረውን ህዝባችንን ፈተናዎች እና ፍላጎቶች ማዳመጥ ቀዳሚ ተግባራችን ነው”፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “በሁሉም አካባቢ የሚኖረውን ህዝባችንን ፈተናዎች እና ፍላጎቶች ማዳመጥ ቀዳሚ ተግባራችን ነው” ሲሉ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ፤ከደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ሲዳማ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ከተወጣጡ ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። በውይይቱም ተወካዮች በልማት ጉዳዮች ላይ አስተያየቶቻቸውን እና ጥያቄዎቻቸውን ማቅረባቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጋራ ግብ ላይ…

Read More

የካራማራ ድል የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ታላቅ ድል ነው

የካራማራ ድል የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት ለማስከበር ዋጋ የተከፈለበት ታላቅ ድል መሆኑን የቀድሞ ጦር ሠራዊት አባላት ገለጹ። የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት በመነጠል ታላቋን ሶማሊያ መመስረት በሚል ዚያድ ባሬ በ1969 ዓ.ም መጠነ ሰፊ ወረራ ማድረጉ ይታወቃል። የሶማሊያ ወታደሮች በወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ዚያድ ባሬ መሪነት በምሥራቅ ኢትዮጵያ 700 ኪሎ ሜትር ዘልቀው በመግባት ወረራ በፈፀሙ ጊዜ ኢትዮጵያውያን የጠላትን ሃይል…

Read More

በክልላችን የተገነባው ‘ኢቲ’ የማዕድን ልማት አክሲዮን ማኅበር የድንጋይ ከሰል ማጣሪያ ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ እንደሚጀምር ተገለጸ

በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው ‘ኢቲ’ የማዕድን ልማት አክሲዮን ማኅበር የድንጋይ ከሰል ማጣሪያ ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ እንደሚጀምር ተገልጿል። የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ ሙሐመድራፊዕ አባራያ፣ የማዕድን ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ብስራት ከበደ እና የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬከተር አቶ ኢጃራ ተስፋዬ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እና የዳውሮ ዞን የስራ ኃላፊዎች የኢቲ የማዕድን ልማት…

Read More

በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት ለቴክኖሎጂ እና አዳዲስ አሰራሮች ትኩረት ተደርጓል – ዶክተር አየለ ተሾመ::

በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋት ቴክኖሎጂ እና አዳዲስ አሰራሮችን ማጠናከር ላይ ትኩረት መደረጉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ ተናገሩ። ሚኒስትር ዴኤታው ይህን ያሉት በአፍሪካ ህብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው ስምንተኛው ሀገር አቀፍ የጤና ኢኖቬሽንና ጥራት ጉባኤ ላይ ነው። ዶክተር አየለ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ በጤና ኤክስቴንሽን፣ በወረዳ ሽግግር እና አጠቃላይ የለውጥ ስራዎች ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል።…

Read More

2 ሺህ የሚሆኑ የቅድመ ወሊድና የወሊድ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በኢትዮጵያ ለመገንባት የሚያስችል የሶስትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሩሲያ የፓን አፍሪካ የመንግስትና የግል አጋርነት የልማት ማዕከል ናቸው የተፈራረሙት፡፡ ስምምነቱ የእናቶችንና የጨቅላ ህፃናትን ህይወት ለማሻሻል የሚረዳ በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ‘ሚድ ዋይፈሪ’ ማዕከል እንደሚሆን ተጠቅሷል፡፡ የሩሲያው የፓን አፍሪካ የመንግስትና የግል አጋርነት የልማት ማዕከል ወደ ሀገር እንዲመጣ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ላበረከተው አስተዋፅኦ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ…

Read More

የአድዋ ድል የአብሮነት፣ የአንድነትና የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት የሆነ አሰባሳቢ ታሪካችን ነው:- አቶ ቀጀላ መርዳሳ

የአድዋ ድል የአብሮነት፣ የአንድነትና የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት የሆነ አሰባሳቢ ታሪካችን ነው ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ ተናገሩ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን 128ኛውን የአድዋ በዓልን “አድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ አክብሯል። የመታሰቢያ በዓሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጀላ መርዳሳ ፣የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ወርቅነሽ ብሩ፣ የተቋሙ ሰራተኞችና አባት…

Read More

የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ሥራዎችን ሰንዶ ማስቀመጥ የተቻለበት ነው-አምባሳደር ብርቱካን አያኖ::

የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይ ለቀጣይ የዲፕሎማሲ ሥራ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ሥራዎችን ሰንዶ ማስቀመጥ የተቻለበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ። አውደ-ርዕዩ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራ ለመዝለቅ ያደረገችውን ጉዞ እና ዲፕሎማሲያዊ ከፍታዋን ያሳየ መሆኑንም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርቱካን አያኖ፤ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።…

Read More

ኢትዮጵያና ኬንያ በቀጣናው ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡ – ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ እና ኬንያ በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥና የኢኮኖሚ ትብብርን ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኬንያ ጉብኝትን አስመልክቶ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ÷ “ኢትዮጵያና ኬንያ ረጅም ጊዜ የቆየ የትብብር፣ የአጋርነት እና የወንድማማችነት ህብረት አላቸው” ብለዋል፡፡ ቀደምት መሪዎች በሰሩት ስራ በሀገራቱ መካከል ግጭቶች እንደሌሉ በመግለጽ፤…

Read More

ኢትዮጵያና ኬንያ የነበራቸውን የቀደመ ግንኙነት የሚያጠናክር ሥራ እየተሰራ ነው ፡- አምባሳደር ባጫ ደበሌ::

በመንግስት በኩል ኢትዮጵያና ኬንያ የነበራቸውን የቀደመ ግንኙነት የሚያጠናክር ሥራ እየተሰራ ነው ሲሉ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ተናገሩ፡፡ ሀገራቱ ረጅም ዕድሜ ያለው ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው፤ ግንኙነቱ እስከ ወታደራዊ ውል ድረስ የዘለቀ እንደነበር አንስተዋል፡፡ ወታደራዊ ውሉ ኢትዮጵያ ችግር ሲገጥማት የኬንያ ወታደር ለኢትዮጵያ እስከ መዋጋት እንዲሁም ኬንያ ችግር ሲገጥማት የኢትዮጵያ ወታደር ለኬንያ እስከ መዋጋት የሚደርስ…

Read More

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓድዋ ድልን አስመልክቶ ሀገር አቀፍ ውይይት እያካሄደ ነው::

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ‘‘ዓድዋ የህብረ ብሄራዊነት ድምቀት የአንድነት ውጤት’’ በሚል ሀገር አቀፍ ውይይት እያካሄደ ነው። ውይይቱ 128ኛውን የዓድዋ ድል ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን ÷ የተለያዩ ፅሁፎችም ቀርበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ዓድዋ የዛሬ 128 ዓመት የተገኘ ድል ብቻ ሳይሆን ለዛሬው ትውልድና ለወደፊቱ ትውልድ ትምህርት የሚሰጥ ነው። የነገዋ…

Read More