Trendings

28ኛው የአድዋ ድል መታሠቢያ በአልን ለማክበር የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ፍፁም ሠላማዊ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል አስታወቀ።

የፀጥታና ደህነት የጋራ ግብረ ሃይሉ የፊታችን የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም የሚከበረው 128ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር ለማስቻል በወጣው የማስፈፀሚያ እቅድ ላይ በአዲስ አበባ ፖሊስ ሰላም አዳራሽ ላይ ውይይት አድርጓል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻ ሀላፊ ጀነራል ተስፋዬ አያሌው በውይይቱ ወቅት እንደገለፁት የመላው ኢትዮጵያውያን በዓል የሆነው የአድዋ ድል በአል ሲከበር ምንም…

Read More

በክልሉ የቡና ምርት የግብይትና ጥራት ቁጥጥር ስርዓትን ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት አለባቸው፦ አቶ ማስረሻ በላቸው::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቡናና ሻይ፣ ቅመማ ቅመም ባለስልጣን የ2016 ምርት ዘመን የቡና ምርትና ግብይት ጥራት ቁጥጥር አስተባባሪ ግበረ-ኃይል የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሄደ። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ቡናን በአግባቡ በማምረት ለአለም ገበያ ማቅረብ የሀገሪቱን ጥቅም ማስከበር በመሆኑ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ዘርፉን ትኩረት ሰጥተው መምራት እንደሚገባቸው…

Read More

የፌደራል ስርዓቱን ለማጠናከር እና የፍትህ ስርዓትን ለማሳለጥ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ::

የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል ፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት የፌደራል ስርዓቱን ለማጠናከር እንዲሁም የፍትህ ስርዓቱን ለማሳለጥ የሚያስችል ስምምነት መፈራረማቸው ተገለጸ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የፌዴራል ፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት በሕግ የተሠጣቸውን ተግባራትንና ኃላፊነቶችን መነሻ በማድረግ የጋራ ግቦቻቸውን ለማሳካት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ዛሬ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ተወያይተው ተፈራርመዋል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር በወቅቱ እንዳሉት…

Read More

ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ በቁጥጥር ሥር የዋለው ከተሰጠው የዘገባ ፈቃድ ውጪ ሲንቀሳቀስ በመገኘቱ ነው፡ – የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ በቁጥጥር ሥራ የዋለው ከተሰጠው የዘገባ ፈቃድ ውጪ በሀገር ውስጥ ጉዳይ ዘገባ ለመስራት ሲንቀሳቀስ በመገኘቱ ነው ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ ለ37ኛው አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ የዘገባ ሽፋን ለመስጠት ፈቃድ አግኝቶ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱን አስታውሰዋል፡፡…

Read More

የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ 23 ነጥብ 46 ቢሊዮን ብር ገቢ አገኘ::

የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በበጀት ዓመቱ አጋማሽ 23 ነጥብ 46 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ። የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክ በ2016 በጀት አመት አጋማሽ በሺፒንግ ዘርፍ ፣ በጭነት አስተላላፊነት ፣ በወደብና ተርሚናል አገልግሎት እንዲሁም በኮርፖሬት አገልግሎት ዘርፍ የተለያዩ ስራዎችን ማከናወኑን ገልጿል። በዚህም በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ከሚሰጡ አገልግሎቶችና ከሌሎች የገቢ ምንጮች 17 ነጥብ 23 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ…

Read More

የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሂደት ሁሉን አቀፍ እንዲሆን መንግስት ቁርጠኛ ነው – ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)::

የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሂደት ሁሉን አቀፍ እንዲሆን መንግስት ቁርጠኛ እንደሆነ የፍትሕ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። የፍትህ ሚኒስትሩ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት በጄኔቫ በጀመረው 55ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ንግግር አድርገዋል። ሚኒስትሩ በቪዲዮ በቀረበ ንግግራቸው፤ የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን በመግለጽ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ አቅርበዋል። የሽግግር…

Read More

የአፍሪካ ልማት ባንክ በኢትዮጵያ በተለዩ የሥራ መስኮች ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ

በኢትዮጵያ በተለዩ የሥራ መስኮች አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን የአፍሪካ ልማት ባንክ አስታወቀ፡፡ በአፍሪካ ልማት ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ሀገሮች ዋና ዳይሬክተር ጆናታን ንዛይኮሬራ ጋር በግብርና ዘርፍ አብሮ መሥራት በሚችሉበት ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በዝናብ ጥገኝነት የሚፈለገውን የግብርና ዘርፍ እድገት ማምጣት እንደማይቻል ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለጀመረችው ስንዴንና ሩዝን በመስኖ የማልማት ሥራ የባንኩ…

Read More

ሕብረተሰቡ ከሐሰት ፕሮፓጋንዳ በመራቅ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት ክልል ለመገንባት እንዲረባረብ ጥሪ ቀረበ::

በአማራ ክልል የተገኘው አንጻራዊ ሰላም የተሟላ እንዲሆን ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ከሐሰት ፕሮፓጋንዳ ራሱን በማራቅ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት ክልል ለመገንባት በጋራ እንዲረባረብ ጥሪ ቀረበ፡፡ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫውም በቀጣይ ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ሰላምን ለማረጋገጥ ውስጣዊ አንድነትንና የውስጥ ሰላምን የበለጠ ማጽናት ይገባል ብሏል፡፡ የክልሉ መንግሥት መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-…

Read More

አሰባሳቢ የወል ትርክቶችን የመገንባትና ሀገራዊ አንድነትን የማጠናከር ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው – አቶ ተስፋዬ በልጅጌ::

አሰባሳቢ የወል ትርክቶችን የመገንባትና ሀገራዊ አንድነትን የማጠናከር ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ ገለጹ። በአዲስ አበባ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ-ከተማ ህዝባዊ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ እንዳሉት ፥ የኢትዮጵያን እምቅ ሃብትና…

Read More

የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች መብት፣ደህንነት፣ተሳትፎና ተጠቃሚነት ተረጋግጧል?

ሪፖርታጂ– አዘጋጅ ዕድገቱ በዛብህ ከጠቅላላው የአገራችን ህዝብ ከ80 በመቶ በላይ የሚሸፍነው ሴቶች ህጻናትና ወጣት የኀብረተሰብ ክፍል ሲሆን ይህም አሃዝ አገራችን ኢትዮጵያ አምራች ሃይል ያላት አገር መሆኗን ያመላክታል፡፡ በመሆኑም ዘላቂ ልማትና ቀጣይነት ያለው ዲሞክራሲ ለማረጋገጥ የሴቶች ህጻናትና የወጣቶች ተሳትፎ ማሳደግና ተጠቃሚነታቸው ማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ባለፉት አመታት ብሄራዊ የሴቶች ፖሊሲ ፤…

Read More