Trendings

37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ተጠናቀቀ::

37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎች በማሳለፍ ዛሬ ማለዳ ተጠናቋል። ጉባኤው “ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“ ሕብረቱ ባዘጋጀው የ2024 መሪ ሀሳብ ከቅዳሜ ጀምሮ ሲካሄድ ቆይቷል። በጉባኤው የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የሕብረቱ ተቋማትና አደረጃጀቶች አመራሮች ተሳትፈዋል።…

Read More

ኢትዮጵያ በ37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በትምህርት ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ድሎች ታንጸባርቃለች::

ኢትዮጵያ በ37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በትምህርት ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ድሎች እንደምታንጸባርቅ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። በጉባኤው ላይ ከአባል ሀገራቱ መሪዎች በተጨማሪ የስድስት ሀገራት መሪዎች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተመላክቷል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ፤ በጉባኤው 49 ሀገራት እንደሚሳተፉ ይጠበቃል ብለዋል። እንዲሁም ከአባላት…

Read More

የአፍሪካ መሪዎች ሙስናን መከላከልና መቆጣጠር ላይ ጠንካራ የጋራ አቋም ሊይዙ ይገባል::

የአፍሪካ መሪዎች ሙስናን መከላከልና መቆጣጠር ላይ ጠንካራ የጋራ አቋም ሊይዙ እንደሚገባ የአፍሪካ ህብረት የሙስና መከላከል አማካሪ ቦርድ ገለጸ። የአፍሪካ ህብረት የሙስና መከላከል አማካሪ ቦርድ የስራ አመራሮች ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። የቦርዱ ሊቀመንበር ሴናቡ ዲካቴ፤ ህብረቱ እ.አ.አ በ2003 ሙስናን ለመዋጋት ያወጣው ስምምነት በአግባቡ ተግባራዊ ባለመደረጉ የሚፈለገው ውጤት አለመምጣቱን አንስተዋል። ቦርዱ የአፍሪካ ህብረት ሙስናን መከላከልና መቆጣጠር ያስችላል…

Read More

ለአቶ ደመቀ መኮንን የጀግና ሽልማት ተበረከተላቸው::

የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን የሰቆጣ ቃልኪዳን የጀግና ሽልማት ተበረከተላቸው። አቶ ደመቀ መኮንን ይህን የጀግና ሽልማት ያገኙት ከ37ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል እየተካሄደ ባለው የሥርዓተ ምግብ ከፍተኛ መድረክ ላይ ነው። ለሽልማቱ ያበቃቸውም ለሰቆጣ ቃልኪዳን እውን መሆንና ገቢራዊነት ላደረጉት ጥረትና ቁርጥ የአመራር ብቃት ነው ተብሏል። በተለይ ደግሞ…

Read More

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የሚቀመጡ ተማሪዎች ምዝገባ እየተካሄደ ነው::

በ2016 ዓ.ም በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የሚቀመጡ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 3 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። አገልግሎቱ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የምዝገባ ሂደትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ዘንድሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ማከናወን የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑን የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ…

Read More

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የተመድ የልማት ፕሮግራም ተወካይ ጋር ተወያዩ::

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) ተወካይ ሳሙኤል ባይድ ዶው ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በአየር ንብረት ለውጥ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ላይ በርካታ ሃብቶችን ማሰባሰብ እና መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡ የተጀመረውን የኢትዮጵያ ስታስቲክስ ልማት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም በተለይ…

Read More

44ኛው የአፍሪካ ሕብረት አስፈጻሚዎች መደበኛ ስብስባ ተጠናቀቀ::

44ኛው የአፍሪካ ሕብረት አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ዛሬ ማለዳ ተጠናቋል። ስብሰባው “ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት“ በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2024 መሪ ሀሳብ ሲካሄድ ቆይቷል። ምክር ቤቱ ከጥር 6 እስከ 17 ቀን 2016 ዓ.ም 47ኛው የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ሀዋሳ ከተማ ገቡ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ በነገው ዕለት በሲዳማ ክልል “ህብረብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ለዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን ህዝባዊ የውይይት መድረክ ለመምራት ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል። እንግዶቹ ሀዋሳ አለም አቀፍ አየር ማረፍያ ሲደርሱ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም…

Read More

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ::

አዲስ አበባ፦ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሰባት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ። አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቶን ገቢና ወጪ ጭነት እንዲሁም ከ115 ሺህ በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ማኅበሩ ጨምሮ ገልጿል፡፡ በማኅበሩ ከፍተኛ የእቅድና የፕሮግራም አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ፍስሐ መብራህቶም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት…

Read More

ሰላም እና ልማት ለኅብረተሰቡ አስፈላጊ ስለሆኑ አንዱ ያለሌላው ሊሳካ አይችልም፡- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ::

በአማራ ክልል የልማት ሥራዎች ዙሪያ የሚመክር የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ውይይት በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። በምክክር ሂደቱ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ እና ሌሎችም የፌዴራል መንግሥት አመራሮች ተገኝተዋል። የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ወደ ክልሉ ለመጡ…

Read More