በብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ ረቂቅ ፖሊሲ ማዕቀፍ ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው::
በብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ ረቂቅ ፖሊሲ ማዕቀፍ ላይ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው። የሽግግር ፖሊሲ የባለሙያዎች ቡድን ላለፉት 8 ወራት የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በማወያየት የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ረቂቅ አዘጋጅቶ ለፍትሕ ሚኒስቴር ማስረከቡ ይታወሳል። በረቂቅ ፖሊሲውም በወንጀል ተጠያቂነት፣ የጊዜ ገደብ እና የሽግግር ፖሊሲውን ለመተግበር የሚያስፈልጉ አዳዲስ ተቋማት ተመላክተውበታል። ሰብዓዊ መብት ተኮር ተግባር፣ ማንንም አለመጉዳት አውድ ተኮር…
