Trendings

ሁሉም የፋይናንስ ሥርዓቶች ደህንነቸዉ የተጠበቀ በመሆኑ ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት መጠቀም ይችላል-ብሄራዊ ባንክ::

በሁሉም የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙ የፋይናንስ ሥርዓቶች ደህንነቸዉ የተጠበቀ በመሆኑ ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት የፋይናንስ አገልግሎቶችን መጠቀም መቀጠል እንደሚችል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ፡፡ ባንኩ አያይዞም አጠቃላይ የፋይናንስ ሥርዓቱ ደህንነት የበለጠ የተጠበቀ፣ አስተማማኝ እና የተረጋጋ ሆኖ እንዲቀጠል አስፈላጊ እርምጃዎችንና የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያዎችን መውሰዱን እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጅታል የባንክ ሥርዓት በጊዜያዊነት መቋረጥን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መግለጫ…

Read More

የመደመር ትውልድ መጽሐፍ በትረካ ለአድማጭና ተመልካች ሊቀርብ ነው

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው የመደመር ትውልድ መጽሕፍ በትረካ፣ በዘጋቢ ፊልምና በሌሎች አማራጮች ለአድማጭና ተመልካቾች ሊቀርብ ነው። አዲስ ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ትረካና ሌሎች ፓኬጆች በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡ በመርሐ ግብሩ የቱሪዝም ሚኒስትር ደኤታ ሌንሳ መኮንን፣ የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ፣ የአዲስ ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ መሃመድ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለአምስት ተቋማት ‘የኢትዮጵያ ተቋማት ስኬት ሽልማትን’ አበረከቱ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዛሬ በአድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደ ደማቅ ስነ-ስርዓት ለአምስት ተቋማት ‘የኢትዮጵያ ተቋማት ስኬት ሽልማትን’ አበርክተዋል። በሽልማቱ የከበሩት ተቋማት የግብርና ሚኒስቴር/በስንዴ ልማት ፕሮግራም/፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት፣ ኢትዮ ቴሌኮም እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መሆናቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ተቋማቱ የኢትዮጵያ የእድገት እና የፈጠራ ልክ ማሳያ…

Read More

የክልሉ የስፖርት ፌዴሬሽኖች የሚያደርገው የጋራ ውይይት መድረክ በታርጫ ከተማ ተካሄደ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ከክልሉ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አመራሮች፣ የክልሉ ስፖርት ፌዴሬሽኖች ፕረዚዳንቶችና ምክትል ፕረዚዳንቶች፣ የባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሃላፊዎች፣ የዞን ፋሲሊቲና አደረጃጀት ሥራ ሂደት ቡድን መሪዎች፣ የቢሮ የስፖርት ዘርፍ ዳይሬክተሮች፣ ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። የምክክር መድረኩ…

Read More

ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካን እየጎበኙ ነው

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የሚገኘውን የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካን እየጎበኙ ነው፡፡ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ፣ የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ (ኢ/ር) እና ሌሎች የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በጉብኝቱ እየተሳተፉ ነው ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡

Read More

የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ ከዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ ከዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ፍሎሪበርት ንጋሩኮ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሩ መንግስት ባለፉት 5 ዓመታት ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዓለም ባንክ የበጀት ድጋፍ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በመተግበር ላይ መሆናቸውን ገልጸው፤ ባንኩ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የምታደርገውን ጥረት ይበልጥ እንዲያግዝ ጠይቀዋል፡፡ ዶክተር…

Read More

ኢትዮጵያ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ እያሳየች ያለችው የላቀ ውጤትና እመርታ ተጠናክሮ ይቀጥላል

ኢትዮጵያ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ እያሳየች ያለችው የላቀ ውጤትና እመርታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ብሔራዊ የአየር ትራንስፖርት ፋሲሊቲ ኮሚቴ ገለፀ። በአየር መንገዱ ላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች የሚሰነዘሩ አሉባልታዎችና የስም ማጥፋት ዘመቻዎች ከእውነታ የራቁና ተቀባይነት የሌላቸው መሆኑም ተጠቁሟል። በአሠራር ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮች ቢኖሩ በጥብቅ ዲሲፕሊንና አሠራር የሚስተካከሉ መሆኑም ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድን የሀገር ከፍታና የመልካም ገጽታ ማሳያነት የሚያስቀጥሉ ዘመናዊ አሠራሮች…

Read More

1445ኛው የረመዳን ወር ፆም ነገ ይጀመራል

1445ኛው የረመዳን ወር ፆም ነገ ሰኞ መጋቢት 2 እንደሚጀመር የሳኡዲ አረቢያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታውቋል። የሳኡዲ አረቢያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በተተከሉ አስራ አንድ አስትሮኖሚ ማዕከሎችን መሰረት በማድረግ ባሰባሰበው መረጃ ጨረቃ መታየቷ አሳውቋል። ይህንን ተከትሎም የረመዳን ፆም ነገ ሰኞ እንደሚጀመር ይፋ አድርጓል። ታላቁን የረመዳን ወር በመተሳሰብና አላህን በመለመን ማሳለፍ እንደሚገባ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች…

Read More

መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል – ዶክተር ለገሰ ቱሉ

መገናኛ ብዙሃን ለሀገር ብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ገለጹ። ከተለያዩ የግል መገናኛ ብዙሃን ለተውጣጡ ጋዜጠኞች በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለአራት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ተጠናቋል። በማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ እና የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መሀመድ…

Read More

ኢትዮጵያ በኢነርጂና አቪዬሽን ዲፕሎማሲ መስክ ትብብር እንዲኖር በትኩረት እየሰራች መሆኑ ተገለጸ::

ኢትዮጵያ በኢነርጂና አቪዬሽን ዲፕሎማሲ ቀጣናዊ ትስስር ለመፍጠር ትኩረት ሰጥታ እየሰራች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም (ዶ/ር)በወቅታዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም ኢትዮጵያ በቀጣናው በኢነርጂና አቪዬሽን ዲፕሎማሲ መስክ ትብብር እንዲኖር እየሰራች መሆኑን ተናግዋል፡፡ በዘርፎቹ መሰል ሥራ ለማከናወንም ኢትዮጵያ ሰፊ አቅም አላት ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፡፡…

Read More