የግሉ ዘርፍ ቱሪዝም ላይ እንዲሳተፍ መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው – ሰላማዊት ካሳ
የግሉ ዘርፍ በቱሪዝም እንዲሳተፍ መንግስት በትኩረት እየሰራ ስለመሆኑ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለጹ፡፡ ሚኒስትሯ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም አዘጋጅነት በሚቀርበው ”ኢትዮጵያ ኢን ፎከስ” ጋር ቆይታ ያደረጉ ሲሆን፥ ስለወቅታዊ የኢትዮጵያ ቱሪዝም እንቅስቃሴ አንስተዋል፡፡ ኢትዮጵያን ለጎብኚዎች ተመራጭ ከሚያደርጓት አንዱና ዋነኛው የተለያዩ ባህሎች፣ መዳረሻዎች፣ ስፍራዎችና ጎብኚዎችን የሚስቡ መስህቦች መኖራቸው ነው ብለዋል፡፡ ማንኛውም ጎብኚ…
