የክልሉ ጤና ቢሮ በክልሉ የጤና አገልግሎቶችን ለማሳለጥ የሚያስችሉ አምቡላሶችን ለዞኖች ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፉን ያስረከቡት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንዳሉት አምቡላሶቹ የእናቶችና ህጻናት ጤናን ለማጎልበት እንዲሁም ለድንገተኛ ህክምና አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸውን ገልፀዋል ። በክልሉ የሚገኙ የጤና ተቋማት ለማህበረሰቡ ጥራት ያለውን አገለግሎት እንዲሰጡ ለማገዝ ቢሮው አስፈላጊውን ሁሉ እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ የጤና አገለግሎቶችን ይበልጥ ለማጎልበትና ተደራሽነትን ለማስፋት ሁሉም የባለድርሻ አካላት ሊተጉ እንደሚገባ ኃላፊው አስገንዝበዋል። ተሽከርካሪዎቹ የእናቶችንና…
