ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የኢትዮጵያን ምርት የመግዛት ባህል ማዳበር ያሰፈልጋል፦ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የኢትዮጵያን ምርት የመግዛት ባህል ማዳበር ይገባል ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር “የኢትዮጵያን ይግዙ” በሚል መሪ ሀሳብ ካዘጋጀው የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽን ጎን ለጎን ትኩረቱን የጥራት መሰረተ ልማት ላይ ያደረገ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት፤ ጥራት ለምርቶች…

Read More

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እና ከጋምቤላ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆች ለተውጣጡ ዲኖች ፣ አሰልጣኞችና ለሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ቴፒ ግቢ ስልጠና መስጠት ተጀመረ።

የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ለሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ዞኑ በተፈጥሮ ሀብቱ የበለፀገ በተለይም በተፈጥሮ ደን፣ በቱሪስት መስህቦች፣ ቡናና ቅመማ ቅመም፣ በማርና በሻይ ምርት የሚታወቅና ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ብሎም ኤክስፖርት በማድረግ ከአካባቢው አልፎ ለሀገር አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልፀዋል። አክለውም ዞኑ ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች…

Read More

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ልማት የግሉን ዘርፍ በስፋት እንዲሳተፍ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አገር አቀፍ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንን ምክንያት በማድረግ “አረንጓዴ ኢኮኖሚን እውን በማደረግ ሂደት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሚና “በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት አካሂዷል። ከውይይቱ ጎን ለጎንም በኃይል ቁጠባ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡና፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሽያጭ የፈጸሙ ኩባንያዎችና ድርጅቶች እውቅና ተሰጥቷል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶክተር)፣ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰሃረላ…

Read More

ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጓል

ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት የቴክኒክና ሙያ የአሰልጣኝ መምህራን አቅም ግንባታ ላይ ትኩረት መደረጉን የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። ሚኒስቴሩ ከነገ ጀምሮ “ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ኃሳብ ለ12 ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እንደሚያስጀምር አስታውቋል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፤ ሥልጠናው አዲስ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ ወደ ሥራ መግባቱን መሠረት ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን…

Read More

በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች እየተከናወነ ያለው የበጎ ተግባራት ዜጎችን በተጨባጭ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል:-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሁሉም አከባቢዎች እየተከናወነ ያለው የበጎ ተግባራት ዜጎችን በተጨባጭ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ገልጸዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተደድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በክልሉ በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀምረዋል።…

Read More

fvfdvg

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ እና የኢፌዲሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ አቅሜ ደካሞች የቤት ግንባታዉን ዛሬ በይፋ በዳዉሮ ዞን በታርጫ ከተማ አስጀምረዋል። የኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከGGGI ከተሰኘው ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የሚያስገነባው አምስት ደረጃቸውን የጠበቁ የመኖሪያ ቤቶች ሲጠናቀቁ በውስጣቸው ሙሉ የቤት ውስጥ…

Read More

በዶክተር መቅደስ ዳባ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በ74ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው

በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በ74ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው። የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ዛሬ ኮንጎ ሪፐብሊክ በብራዛቪል መካሄድ ጀምሯል። እስከ ነሀሴ 25/2016 ዓ.ም በሚቆየው መድረክ በጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክም በመድረኩ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። ዛሬ በብራዛቪል ከተማ በይፋ በተጀመረው 74ኛው…

Read More

የንግድ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ነው – ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)

የንግድ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ የተደገፈና የተደራጀ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ። ዛሬ የአገር ውስጥ ንግድን የተመለከተ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱ ላይ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፣ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት፣ ምሁራን፣ የሸማች ማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል። የንግድ ስርዓቱ ከብልሹ አሰራሮች የፀዳና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ሚኒስትሩ…

Read More

በሳሙኤል ኡርቃቶ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በብሪክስ የስፖርት ዘርፍ መድረክ እየተሳተፈ ነው

በፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በብሪክስ የስፖርት ዘርፍ መድረክ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የብሪክስ አባል ሀገራት የስፖርት ዘርፍ መድረክ በስፖርት ዘርፍ የሚስተዋለውን ሙስና እና ብልሹ አሰራር በመከላከል ዙሪያ የሚመክር መድረክ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በመድረኩም የፌዴራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶን (ዶ/ር) ጨምሮ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ…

Read More