ኢትዮጵያ ለአንካራው ስምምነት ተግባራዊነት ቁርጠኝነቷን ስትገልፅ፤ ሶማሊያም በበኩሏ ስምምነቱ በተፋጠነ ሁኔታ እንዲተገበር እሻለሁ ብላለች
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ዲኤታ አሊ መሐመድ ኡመር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። አምባደሳደር ምስጋኑ በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ህዝቦች የማይነጣጠል መፃኢ ዕድል ያላቸው መሆኑን በመግለፅ፤ ሀገራቱ ተባብረው መስራት፣ ችግሮች ሲጋጥሙም ተቀራርቦ መፍትሄ መሻት ይገባቸዋል ብለዋል። ኢትዮጵያ ለአንካራው ስምምነት ተግባራዊ መሆን ቁርጠኛ…
