የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ዘርፍን ለማጠናከር ያለመ ዉይይት በዳዉሮ ዞን ተካሄደ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት በዳዉሮ ዞን የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ በዳውሮ ዞን ተካሂዷል። በክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ በአቶ የሺዋስ ዓለሙ የተመራ የአመራር ቡድን ከዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በየደረጃው የሚገኙ የኮሙኒኬሽን መዋቅሮችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ሰፊ ምክክር አድርጓል። የሚዲያ ሚና ለልማት ስኬት ወሳኝ ነው አቶ…

Read More

የምግብ ስርዓት ለውጥ ፍኖተ ካርታና ክላስተር 7 ማስተዋወቂያ ስልጠና በቦንጋ ከተማ ተጀመረ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምግብ ሰርዓትና የስርዓተ–ምግብ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ዩኒት ከአግሪካልቸራል ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት (ATI) ጋር በመተባበር በ“የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን የፍኖተ ካርታ ወርክሾፕ እና ክላስተር 7 ግንዛቤ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ የውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ፕሮግራም በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናው በክልሉ የምግብ ስርዓትን በዘላቂነት፣ በተቀናጀ አቀራረብ እና በክላስተሪንግ ስርዓት ለመለወጥ የሚያግዙ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ላይ…

Read More

በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው ብሔራዊ መግባባትን ለማጠናከር በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ኮሚሽኑ በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የተከናወኑ ተግባራትን ገለፃ አድርገዋል። ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው የግጭት አዙሪት የተሳሳቱ መንገዶች በሀገራዊ ምክክር መፍትሔ ሊያገኙ እንደሚገባ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል። ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን…

Read More

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

መንገድ ትራፊክ አደጋ መጠን ለመቀነስና የማሽከርከር ስነ-ባህርይ ላይ በክልላችን ሁሉም ዞኖች የነባር አሽከርካሪዎች ተሃድሶ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት የቢሮ ምክትል ኃላፊና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ኢንጅነር ዘመዴ አንዳርጌ እንዳሉት በክልሉ ለ19 ሺህ ነባር አሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና በ32 ማዕከላት እየተሰጠ እንደሆነ ገልጸዋል። ኃላፊው ስገልፁ በግል በማህበራትና በመንግስት ተቋማት ሥር…

Read More

ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር የሆኑትን ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት ሹመትን አፀደቀ። ምክር ቤቱ ለኮርፖሬሽኑ ቦርድ አባልነት የቀረቡ ዘጠኝ ዕጩዎችን ሹመት አፅድቋል። በዚህም፦ ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት – የቦርዱ ሰብሳቢ (የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ…

Read More

የዲዚ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የምስጋና በአል “ከያ ቢያርግ” መከበሩ ባህላቸውን ወደፊት እንዲወጣ እድል እንደፈጠረላቸው የቤሮ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

በአሉን የማስተዋወቅ ወደፊት የማውጣት ስራ ተጠናክሮ እንደሚሰራ የቤሮ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አራጋው ይመር አስታውቀዋል። የዲዚ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በአል “ከያ ቢያርግ” የተጣላ የሚታረቅበት፣ የደረሰ እህል የሚቀመስበት፣ ለቀጣይ አዝመራ የእርሻ መሳሪያዎች ለእርሻ የሚዘጋጁበት በመሆኑ በአሉ በብሔረሰቡ ዘንድ ታላቅ ትርጉም ያለው መሆኑ ተጠቁሟል። በአሉ በባለፉት ሀምሳ አመታት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን ዘንድሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።…

Read More

ተቋማዊ አቅምን በመገንባት የመረጃ ተደራሺነትን ለማረጋገጥ የተሰራዉ ሥራ አበረታች መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት ገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ፣ መረጃን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግና ተቋማዊ አሠራርን ለማዘመን የጀመራቸው ሥራዎች ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት የማኅበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴው የቢሮውን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የሥራ አፈፃፀም በገመገመበት ወቅት እንደተገለጸው፤ ተቋሙ የመረጃ አቅርቦትን ጥራት ለማረጋገጥና የቴክኖሎጂ አማራጮችን ለማስፋት የሄደበት ርቀት አበረታች ነው። በግምገማ…

Read More

በክልሉ ዘላቂ የጤና፣ ምግብና የትምህርት ልማት ሥራዎችን ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት የተባበሩት መንግስታት የዓለም ዓቀፍ የልማት አጋር ድርጅቶች ገለጹ

የተለያዩ የተባበሩት መንግስታት የዓለም ዓቀፍ የልማት አጋር ድርጅቶች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የቀጣይ ድጋፍ አቅጣጫ ለመለየት ያለመ የልማት ሥራዎች ጉብኝት እና ከክልሉ መንግስት ጋር ውይይት ማድረጋቸው የሚታወስ ነዉ። የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) የኢትዮጵያ ተወካይ ዶ/ር ፍራንሲስ ቺሳካ፤ በክልሉ በነበራቸው ቆይታ በክልሉ ያለውን እምቅ አቅም መመልከታቸውን ገልጸዉ በተለይም በትምህርት ቤቶች የተመለከቱት የተማሪዎች ምገባ መርሐግብር…

Read More

ዓለም በአንድ ድምፅ ስለ አንድ ጉዳይ ይነጋገራል፣ ትንበያዎችን ያስቀምጣል፣ ስጋቶችን በጥናት አስደግፈው ይጠቁማል። ነገር ግን በየቀኑ አባባሽ መንስኤዎችም እየጨመሩ ቀጥለዋል።

ካደጉት ሀገራት የሚለቀቁ በካይ ጋዞች አማካኝነት በሚከሰት አየር ንብረት ለውጥ መዛባት ምድራችን ሲትናጥ: በታዳጊ ሀገራት ደግሞ በአካባቢ አያያዝና ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ክፍተቶች ትፈተናለች። እንደ ሀገር ይኸንኑ ችግር መቋቋም በሚያስችል መልኩ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ አረንጓዴ አሻራ እና ጽዱ ኢትዮጵያ የመሳሰሉ ንቅናቄዎች ተግባራዊ ሆነው ውጤትም እየተመዘገበ ይገኛል። በዚህ ጉዳይ ላይ የክልሉን ተጨባጭ አሰተዋጽኦ በሚመለከትና የሚንታወቅበትን የተፈጥሮ ሀብት…

Read More

የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን ደርሷል

የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን ደርሷል የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁ ጥር 97 ሚሊዮን መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው በመንግሥት የ6 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የዲጂታል ዘርፉ በተለይም የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚነት…

Read More