ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የአምራች ኢንዱስትሪ ማምረቻ ማዕከል መርቀው ከፈቱ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ በክልሉ መንግሥት የተገነባውን የአምራች ኢንዱስትሪ የማምረቻ ማዕከል መርቀዋል። ፕሮጀክቱ በቀድሞው የደቡብ ክልል ጊዜ ተጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው የተጓተተ ቢሆንም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምሥረታ ማግስት÷ የክልሉ መንግሥት ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቀው ለኅብረተሰቡ ተገቢውን አግልግሎት እንዲሰጡ በሰጠው ልዩ ትኩረት ተጠናቆ ለምርቃት…
