ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ ተቋማት የተግባር አፈጻጸም በመገምገም፣ ክፍተቶች በመለየት የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እያስቻለ ነዉ:-የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ በታርጫ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በጉባኤው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ ዋና አፌጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ÷ ምክር ቤቱ ባለፊት የበጀት ዓመት ስድስት ወራት የአስፈጻሚ ተቋማት የተግባር አፈጻጸም በመገምገምና ክፍተቶችን በመለየት የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የበኩሉን ሚና መወጣቱን ገልጸዋል። የታችኛው…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የቴሌቪዥን ሙከራ ሥርጭት ጀመረ

የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የቴሌቪዥን ሙከራ ሥርጭቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ ጀምሯል። ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ዶ/ር) በማስጀመሪያው ወቅት እንደገለጹት፤ ሚዲያ ኔትዎርኩ በክልሉ ያለውን እምቅ ሀብት፣ የማህበረሰቡ ብዝሃ ማንነት፣ ቋንቋና ወግ ከሀገር አልፎ በዓለም ደረጃ እንዲተዋወቁ በትኩረት እንዲሰራ አጽንኦት ሰጥተዋል። ከክልላዊ አንድነት ባሻገር ህብረብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮችን የሚዲያና ጋዜጠኝነት…

Read More

ጠንካራ ተቋማት ግንባታና አደረጃጀት ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል የሀገረ መንግሥት ግንባታን ለማፋጠን በትኩረት እየተሰራ ነው፦ አቶ ፍቅሬ አማን

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በኮንታ ዞን ለሚገነባው የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ህንፃ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ብልጽግና ፓርቲ በሀገራችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ና በተቋም ግንባታ ስር የሰደዱ ሰብራቶችን በመጠገንና በማከም በርካታ ስኬቶችና ድሎችን ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል። እነዚህ ስኬቶች የህዝቡን ሁለንናዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ…

Read More

ድል የቀናው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር በአዳማ

ስፖርታዊ ውድድር በዜጎች መካከል ማህበራዊ ትስስርና አንድነት በማጠናከር ለማህበራዊና ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ሚናው የጎላ መሆኑን የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ ‌‎በኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በኦሮሚያ ክልል አስተናጋጅነት ሀገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ስልጠና ምዘና ውድድር “የታዳጊ ስፖርተኞች ልማት ለኢትዮጵያ ከፍታ”በሚል መሪ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ‌‎ ‎ውድድሩ እንደአገር በ15 የስፖርት አይነቶች እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን…

Read More

የብሔረሰቡ ቋንቋና ታሪክ ላይ በደንብ ለመስራት የተቀናጀና ቀጣይነት ያለውን ሥራ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ

የማጃንግ ብሔረሰብ የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም የብሔረሰቡ ተወላጆችና ወዳጆች በተገኙበት በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ፓናል ውይይት አካኺዷል ። የፓናል ውይይቱን መነሻ ነጥቦች የሚጠቁም ሰነድ ያቀረቡት የደቡብ ምዕራብ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ጸ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እንዳሻው: ብሔረሰቡ ከጥንት ጀምሮ የራሱ የሆነ ባህላዊ ክዋኔ፣ ቋንቋ፣ ወቅትና ወራት አቆጣጠር ያለው ህዝብ መሆኑን አሳይተዋል። በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ አያያዝ እስከ…

Read More

በሚዛን አማን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መከፈቱ የአካባቢውን ማህበረሰብ የሚያወጣውን ገንዘብና የሚያባክነውን ጊዜ እንደሚቆጥብ ተገለፀ።

​በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የሚዛን አማን ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት መከፈቱ፣ አገልግሎት ፈላጊዎችን ለከፍተኛ እንግልትና ወጪ ሲዳርግ የነበረውን ጉዞ እንደሚያስቀር የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጀማል ደስታው ገለጹ። ​ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ መደበኛ አገልግሎቶችን መስጠት መጀመሩን አቶ ጀማል ጠቁመው ዜጎች የፓስፖርትና ሌሎች ተያያዥ አገልግሎቶችን በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ ለማድረግ ተቋሙ በሰፊው እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ​እንደ አቶ ጀማል ገለጻ፣ ተቋሙ ሀገራዊና…

Read More

ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሌሴቶና ሞሮኮ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከሌሴቶ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሌጆን ምፖትጆአኔ እና ከሞሮኮ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናስር ቡሪታ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ጌዲዮን (ዶ/ር) ከሌሴቶ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሌጆን ምፖትጆአኔ ጋር ባደረጉት ውይይት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ውጤታማ በሆነችባቸው ዘርፎች ለሌሴቶ ልምዷን ለማካፈል ዝግጁ እንደሆነች መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡…

Read More

የክልሉ መንግስት መስተዳድር ምክር ቤት 47ኛ መደበኛ ስብሰባዉን በሃለላ ኬላ አካሂዷል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት መስተዳድ ምክር ቤት ዛሬ በሃላላ ኬላ ባካሄደዉ 47ኛዉ መደበኛ ስብሰባ በ1ኛ አጀንዳነት የተመለከተዉ የክልሉ መንግስት የአስፈጻሚ ተቋማት የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈጻጸም ገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ በመሉ ድምጽ አጽድቋል። ምክር ቤቱ በ2ኛ አጀንዳነት የመንግስት ፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት ለመወሰን የወጣ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ አስተያየት በመስጠት ወደ ምክር…

Read More

የማጃንግ ብሔረሰብ ውብ ባህል ያለውና ከሌሎች ህዝብ ጋር አብሮ የመኖር የዳበረ ልምድ ያለዉ ህዝብ ነው:- አቶ አበበ ማሞ

የማጃንግ ብሔረሰብ የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም የብሔረሰቡ ተወላጆችና ወዳጆች በተገኙበት በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በፓናል ውይይት ተጀምሯል ። የብሔረሰቡን ቀደምት እሴቶችን ለማነቃቃትና ለማልማት ያለመው የመጀመሪያውና ታሪካዊው የየቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም: ቱባ ባህሉ ይዘቱን ጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድና ለዓለም ለማስተዋወቅ መሠረት የሚጣልበት ታላቅ ቀን መሆኑ ተመላክተዋል። በሲምፖዚየሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ የለውጡ…

Read More

48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ

48ኛው የአፍሪካ ሕብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። በስብሰባው የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ፣ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስን (ዶ/ር) ጨምሮ የሕብረቱ አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች፣ የሕብረቱ ተቋማት አመራሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ ዛሬና ነገ ለሁለት…

Read More